Mar 29, 2013

! ….. ‘ህወሓት ለህዝብ ሮሮ ጀሮ የለውም’ …!


ህወሓቶች በ9ኛው የኢህኣዴግ ጉባኤ ተሸማቀው መመለሳቸው ተሰምተዋል። በሁሉም የኢህኣዴግ ኣባል ድርጅቶች
ኣለመተማመንና እርስበርስ መናናቅ ቢስተዋልም ህወሓቶች የለመዱቱን ‘ክብር’ በመነፈጋቸው (የሚያቀርቡት ሓሳብ ሲብጠለጠል በማየታቸው) እጅግ እንዳዘኑና እንዳፈሩ ለማወቅ ተችለዋል።

ድሮም ቢሆን እነዚህ ተራ የህወሓት ኣባላት (የኣሁኑ መሪዎች ማለቴ ነው) ከሌሎች የድርጅት መሪዎች በቀጥታ (የሓሳብ) ክርክር ኣድርገው ኣያውቁም። በመለስ በኩል ነበር የሚገናኙ። መለስ ለየብቻቸው ያሳምናቸው ነበር። ኣሁን ይሄን ሚና የሚጫወት የለም። እናማ ህወሓቶች ተንቀናል (ተሰሚነት ኣጣን) ብለው ኣኮረፉ፣ ኣፈሩ። በትክክል ውርደት ነው። ኣንድ ተሳታፊ ‘ ቢስቢስ እኮ አሎምና’ (ትግርኛ) ብለዋል።

እንደዉጤቱም ከጉባኤው መልስ በትግራይ በኣብዛኛው የክልል መንግስት መስርያቤት በስብሰባ ተጠምደዋል። ትናንት (ሓሙስ መጋቢት 19, 2005) የመንግስት ሰራተኞች ስራቸው ትተው ስብሰባ ዉለዋል። የመንግስት ስራ ትተው ለፓርቲ ስብሰባ መጥራት ተገቢ ኣልነበረም።

እነሱ ስልጣናቸውን የሚያራዝሙበት ስብሰባ (የህዝብ ጅንጀና) ሲያካሂዱ ህዝቡ (ተገልጋዩ) ግን የፍትሕ ግልጋሎት ኣጥቶ ሲሰቃይ ማየት ያሳዝናል።

የመኾኒ ነዋሪዎች መኖርያ ቤታቸው እንደሚፈርስ ተነግሯቸዋል። በቅርብ ግዜ ወደ 7 ሺ ቤቶች ይፈርሳሉ (ገጠሩ ጨምሮ መሆን ኣለበት እንጂ 7ሺ ቤቶች በመኾኒ ከተማ ይኖራል ብዬ ኣልገምትም)። በመጀመርያ ዙር 1500 ቤተሰብ ይፈናቀላል። ይቀጥላል።

እነዚህ ነዋሪዎች መኖርያ ቤታቸው ሲፈርስ ሌላ ኣማራጭ መጠልያ ስለሌላቸው መንግስት መፍትሔ እንዲያፈላልግላቸው ለወረዳው ኣስተዳዳሪዎች ኣቤት ብለው ነበር። መትፍሔ ኣላገኙም። ችግሩ ያስጨነቃቸው ነዋሪዎች ከ150-200 የሚሆኑ ተወካዮች መርጠው ወደ ክልል መንግስት ቢሮ (መፍትሔ ፍለጋ) ላኩ።

የክልል መንግስት ሓላፊዎች ወደ ወረዳቸው እንዲመለሱ ያዛሉ። ‘የወረዳ ኣስተዳዳሪዎችማ መፍትሔ ሊሰጡን ኣልቻሉም፣ ለዚህ ነው ወደ ክልል የመጣነው።’ ተወካዮቹ ይመልሳሉ። የክልሎችም ‘እኛ የምናውቀው ነገር የለም’ በሚል ከኣከባቢው እንዲርቁ ያስገድዷቸዋል።

የነዋሪዎቹ ጥያቄ ምንድነው? “ኣንደኛ ቤታችን የሚፈርሰው ኣለኣግባብ ነው። ሁለተኛ መኖርያችን መንግስት በሃይሉ የሚያፈርሰው ከሆነ ሌላ ኣማራጭ መጠልያ ልያዘጋጅልን ይገባል።” ይላሉ። በተጨማሪም “መንግስት ለውጭ ዜጎች (ለምሳሌ የኤርትራ ስደተኞች) መጠልያ ያስፈልጋቸዋል ብሎ የተለያዩ ነገሮች ሲያዘጋጅላቸው ለኛ (ለዜጎቹ) ግን ያለ ምንም ኣማራጭ መኖርያችን ለማፍረስ እየተዘጋጀ ነው” ብለው ይከሳሉ።

የክልል ባለስልጣናት መፍትሔ ስላልሰጡዋቸው (ባለስልጣናቱ ለግል ወይ ፓርቲ ስብሰባቸው እንጂ) ለህዝብ ፍትሕ ወይ ግልጋሎት ደንታ ስለሌላቸው ተወካዮቹ ወደ ዓረና ትግራይ ፓርቲ መስራቤት በመሄድ ጉዳያቸውን ማስረዳታቸው ሰምቻለሁ። ሰዎቹ ከመኾኒ- መቐለ ለሳምንት ያህል መመላለሳቸው ገልፀውልኛል። የመንግስትም የግልም የሚድያ ሽፋን ኣለማግኘታቸው ያሳዘናቸው ይመስላል። በመጨረሻም ‘ህወሓት ለህዝብ ሮሮ ጀሮ የለውም’ የሚል ኣስተያየት ሰንዝረዋል።

እባካቹ ህወሓቶች ከመንግስት ስራ የፓርቲ ስብሰባ ኣታስቀድሙ። የመንግስት መስራቤትም ለፓርቲ ስራ ማዋል ሙስና ነው። የፓርቲና የመንግስት ስራ የተለያዩ ናቸው። ቅድምያ ለህዝብ ስጡ። ያለ ህዝብ ስልጣን የለም፣ ሃብት የለም፣ ‘መከበር’ የለም። ሁሉም ነገር የሚያደረው ህዝብ ነው።

ለህዝብ ቅድምያ እንስጥ።

It is so!!!

Mar 28, 2013

“ሀገሬ ገመናሽ” (ዶክተር በድሉ ዋቅጅራ፣ ክፍል ሁለት)



በየፍርድ ቤቶችሽ የፍትህ ውርጃ ሲፈፀም ዝም አልሽ።
ዶክተር በድሉ ዋቅጅራ
ልዕልና ጋዜጣ
ምንጭ፣ ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም ብሎግ
በቀደም ሳት ብሎኝ፣
ለመጀመሪያ ልጄ ብቻ የፈረንጅ ሸራ ጫማ ገዝቼ ገባሁ። ያለወትሮዬ ማለቴ ለወትሮው ገበያ የምወጣው ሁለቱንም ልጆቼን ይዤ ስለነበረ ነው። ታዲያ ያን እለታ ማታ ትልቅዋ ልጄ ጫማውን ስትለካ፣ የታናሽ እህትዋ አይን ከሚለካው ጫማ ጋር ሲንከራተት ተመለከትኩ፤ ወይም የተመለከትኩ መሰለኝ። ‹‹ከወደድሽው ላንቺም ይገዛልሻል››አልኳት፤ የትንሽዋን ልጄን አይን እየሸሸሁ። በውስጤ አድሏዊነት ተላወሰ። በልጅትዋ ህሊና ውስጥ ይህ ስሜት እንደማያድር ባውቅም፣ የእኔን ሃሳብ ግን ቶሎ ላስወግደው አልቻልኩም። አየሽ ሀገሬ? እንኳን ህዝበ አዳምና ሔዋንን በእኩልነት ቤት ሆኜ አኖራለሁ የሚል ሀገር፣ አንድ ተራ ምስኪን ወላጅ እንኳን በጎጆው አድሏዊነት እንዳይሰፍን ይጥራል። አንቺ ግን ሀገሬ! … አንቺ ግን ዝሆንና ጥንቸል እያፋለምሽ ለአሸናፊው ታጨበጭቢያለሽ፤ ትሸልሚያለሽ።
መቼም ማንም ቢሆን፣ የአደባባይ ውበቱን እንጂ የጓዳ – ጎድጓዳ ገመናውን ሲነግሩት አይወድምና አንቺም ከአደባባይሽ ጀርባ መዝለቄ እንደማይጥምሽ አውቃለሁ። አደባባዮችሽማ ለዜጎችሽ የጋራ ፍትሀዊ መኖሪያነትሽን ይመሰክሩልሻል። መቼም የዜጋ ሁሉ እኩልነት የሚረጋገጠው በህግ ፊት ባለው እኩል መብት አይደል? ይህ ደግሞ ከገጠር ቀበሌሽ አንስቶ እስከ መዲናሽ ባሉ አደባባዮችሽ የሚታይ ነው። የወረዳ ፍርድ ቤት፣ የዞን ፍርድ ቤት፣ የክልል ፍርድ ቤት፣ የፌደራል ፍርድ ቤት፣ ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ሰበር ሰሚ ችሎት… የፍትህ ቢሮ… ይህ ሁሉ አደባባይሽን ያደመቅሽበት የዜጎችን እኩልነት ማስጠበቂያ ተቋም ነው። ሀገሬ! ለመሆኑ በእነዚህ ተቋማት ምን እያደረግሽ እንዳለሽ ታውቂያለሽ?
አንዳንዴ ሳስበው ፍርድ ቤቶችሽና የፍትህ ተቋማቶችሽ ለዜጎች እኩል ያለመሆናቸውን የምታስታውቂበት ስፍራ ይመስለኛል። ይህን ስትሰሚ እንደምትቆጪ አውቃለሁ። ገመናው ሲሸፈንለት እንጂ ሲገለጥበት የሚወድ ማን አለ! አሁን እስቲ አንቺ ህግ አቁሜያለሁ፣ ዳኛ ሰይሜያለሁ ትያለሽ? ሀገሬ ሙች አፍሽን ሞልተሸ አትይም። ምነው ብትይ እማኝ ጠቅሼ እሞግትበት ሞልቶኛል።
አንድ አትዮጵያዊ ለትምህርት ውጭ ሄዶ ሳለ፣ በፈቀድሽው ከታክስ ነፃ መብቱ ተጠቀመና አውቶሞቢል ገዝቶ መጣ። አንቺንና ያቆምሽውን መንግስት እያሞገሰ አራት አመት በአውቶሞቢሉ ተጠቀመና ተመልሶ ለትምህርት ሄደ።
ባለቤቱ ደግሞ አሁንም አንቺንና መንግስቷን እያመሰገነች ስትነዳ፣ አንድ ቀን በጉምሩክ አሳሽ ጓዶች ተያዘች። መቼም ‹‹ለምን?›› ማለትሽ አይቀርም። የመኪናው ሊብሬ በባለቤትዋ ስም ስለነበር፣ አንቺ በአውቶሞቢሉ መገልገል አትችይም ተብላ፣ ተያዘች። መኪናው ታሰረ። አጣሪ ተቋቋመ። አጣሪው አጣርቶ ‹‹ባለመብቱ ባለቤትዋ በመሆኑ፣ በአውቶሞቢሉ መጠቀም መብትዋ ነው›› ብሎ ሪፖርት አቀረበ። ኮፒው ደግሞ ለሴትየዋ ደረሰ። ታዲያ ሀገሬ ጉዳዩ የቀረበለት የጉምሩክ ባለስልጣን፣ ቀረጡን ትከፍያለሽ አላት። ተያይዞ የቀረበውን ሪፖርት ተመልክቶት እንደሁ ጠየቀችው። አለመመልከቱን፣ ቢመለከተውም እንኳን ሪፖርቱ እግዚአብሔርም ቢመጣ ከመክፈል እንደማያስጥላት፤ ካልከፈለች መኪናዋ ጉምሩክ ውስጥ እንደሚታሸግበት ነገራት።  ሀገሬ፣ ሴትየዋና ባለስልጣኑ ሁለቱም ያንቺ ዜጎች፣ ሁለቱም ኢትዮጵያዊ ናቸው። ቆይ ህግሽ ላይ ‹‹አንድ ኢትዮጵያዊ›› የሚለው ሀረግ ማንን አስበሽ ያሰፈርሽው ነው? እና ሴትዮዋ ሃምሳ አራት ሺህ ብር ከፈለች። ከመክፈልዋ በፊት ግን ሀገሬ ሙች አልቅሳ ለምናዋለች። ከእግዚአብሔር በላይ ያስቀመጥሽውን ዜጋ መለመን እንጂ ምን መፍትሔ አለ! ባለቤትዋ ይህን ሲሰማ መጀመሪያ ያዘነው ባንቺ አይደለም። ባስቀመጥሽው ባለስልጣን ትእቢትና ድንቁርና ተደነቀ። ህግ ፊት አቅርቦ፣ ባለቤቱ በህግ የተሰጣትን መብት የሚጥስበት ከህግ የከበረ መብት እንደሌለው ሊያሳየው፣ ባለስልጣኑን ህግ ፊት ሊገትረው ከአውሮፓ ሲበር መጣ፤ ጠበቃ ቀጠረ።
በቀጠሮው ቀን እሱና ጠበቃው ማልደው ፍርድ ቤት ደረሱ። ተከሳሽ አልቀረበም። የመስሪያ ቤቱ ጠበቃ እንኳን አልቀረበም። ዳኛዋ ሌላ ቀጠሮ ሰጡ። በቀጠሮውም ቀን የቀረበ የለም። ዳኛዋ ባለስልጣኑ ፍርድ ቤቱን ማዋረዱን፣ ከአንዴም ሁለቴ በቀጠሮ አለመቅረቡን ከምንም ሳይቆጥሩ ፍርዱን ገመደሉት። ባለስልጣኑ ትክክል መሆኑን፣ ሴትየዋ መያዛቸው፣ ገንዘቡንም መክፈላቸው አግባብ መሆኑን ፈረዱ።
ሀገሬ፣ ያ ከአውሮፓ የፍትህ ጥማት ሲያበር ያመጣው ሰው፣ በፍትህ መዶሻሽ የተጨፈለቀ ዜግነቱን ይዞ ወደአውሮፓ ተመለሰ። አየሽ ሀገሬ! ለዚህ ነው የምሞግትሽ፤ እኛን ዜጎችሽን ከወባ፣ ከተስቦ ብትፈልጊም ከኤች.አይ.ቪ በላይ የጎዳን በየፍርድ ቤትሽ በህግ የበላይነት ለማያምን  ዳኛ ያስጨበጥሽው መዶሻ ነው።
እንዴ እውነቴን እኮ ነው! ሀገሬ ሙች እውነቴን ነው። ለወባው፣ ለተስቦውና ለኤች.አይ.ቪ.ው እድሜ ለቱጃሮቹ ጓደኞችሽ እንጂ፣ መች መድሀኒት ይገደናል- መርከብ ሞልተው ይልኩልናል። ደግሞ ብንሞትስ! እድር አለን እንቀበራለን። ቆይ እድር ባይኖረንስ! ደግሞ ለመቅበር! አበሻ እንኳን ሞተሽለት ገና በጣር ተይዘሽ፣ ላይ ላዩን መተንፈስ ስትጀምሪ ነው ጉድጓድ መቆፈር የሚጀምረው። ግን ሀገሬ እንዲህ በቁማችን በፍትህ መዶሻሽ ስንሰባበር፣ እነዚህ የወባና የተስቦ መድሀኒት በመርከብ ሞልተው የሚልኩልን ጓደኞችሽ አንቺንም ሆነ መንግስትሽን ሀይ አላሉልንም። እና ሀገሬ፣ ይህ የአንቺ ብቻ ሳይሆን የነሱም ገመና ነው።
ቆይ እኔ የምለው መንግስት ከህግ በላይ ነው እንዴ!? እስቲ ንገሪኝ ሀገሬ- መንግስት የሆኑት ከእኛው መሀከል፣ እንደኛው ዜጋ የነበሩት አይደሉም እንዴ! ዜጎችሽ አይደሉም እንዴ ‹‹መርጣችሁናል›› ብለው መንግስት የሆኑት! ታዲያ ለምንድነው የፍትህ መዶሻሽ እነሱ ላይ ቄጠማ የሚሆነው? ይኽው በአንቺ ውስጥ ከልጅነት እስከ እውቀት ስኖር መንግስት ከሳሽም ተከሳሽም ሆኖ ሲረታ እንጂ ሲፈረድበት አይቼም፣ ሰምቼም አላውቅም። ምን ያስቃል ሀገሬ! በእርግጥ ገንዘብን፣ ወይም ደግሞ ሌሎች ቀለል ያሉ ጉዳዮችን በተመለከተ አንድ ሁለት ፋይሎች በመንግስት ካሳ ከፋይነት እንዲዘጉ አድርገሽ ሊሆን ይችላል። ይህን ተይና እውነት ሀገር ከሆንሽ፣ እስቲ በሰብአዊና በዜግነት መብት ጉዳይ መንግስትን ከስሶ ያሸነፈ አንድ ዜጋ ጥሪ! እረ ጉደኛ ነሽ፣ ሀገሬ!
እኔ የምልሽ የህግ ትምህርት ቤት፣ ምናምን ምን ያደርግልሻል? ለምን አምስትና ስድስት ዓመት ህግ ታስተምሪያለሽ? ለእኛ ለዜጎችሽ ያቆምሽው፣ ህግ እንዳይዛነፍ፣ በየፍርድ ቤቱ ያስቀመጥሽው መዶሻ አናት አናታችንን እያለ ቅስማችንን እየሰበረ፣ ከዜግነት ተራ እንዳያስወጣን አይደለም እንዴ! በአንቺ በሀገሬ ህግ፣ እንኳን መርጠኽኛል፣ ያለ ባለስልጣንና መንግስት ቀርቶ፣ እየሱስ ክርስቶስም ቢሆን፣ ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ አብሮኝ ቢኖር፣ በህግ ፊት እኩል ነን። አቦ ሀገሬ በፍትህ ስም የምትሰሪው ግፍ በዛ! የምር በዛ። ወይ በቃ የህግ ትምህርት ቤቶችሽን ዝጊና ዳኛ ለምታደርጊያቸው ዜጎች እንዴት የባለስልጣንንና የመንግስትን የስልክ ትእዛዝ ተቀብለው ተግባራዊ ማድረግ እንዳለባቸው አንድ ሁለት ሳምንት አሰልጥነሽ … በቃ!
አንዳንዴ ሳስበው ያ ታከለ የሚመኘውን ምኞት እኮ ሁላችንም ልንመኘው ነው! ሀገሬ መቼም ታከለን ታውቂዋለሽ። ለነገሩ አንዳንዶቹን አውቀሽ ችላ ትያቸዋለሽ እንጂ፣ አንቺ ዜጋሽ መቼ ይጠፋሻል። እሱም አንዱ ፍትህ መከበር አለበት፤ ያለ ህግ የበላይነት ሀገርና ህዝብ አይቆምም፣ ባይ ነው። ታዲያ የውልሽ፣ ከአመት ተመንፈቅ በፊት የቢ.ፒ.አር አሰራሩን ተቃውመሀል ተብሎ ከስራ ታገደ። ሁለት ወር ያለ ስራ ደመወዝ በላ። በሶስተኛው ወር ደመወዙ ቆመ። ሀላፊውን ሊያነጋግር ሄዶ የስራ መልቀቂያ ደብዳቤውን ተቀብሎ መጣ። ታዲያ ያን ሰሞን እቤቴ መጣና፣ ‹‹ገንዘብ አበድረኝ›› ሲለኝ፣ ያው እንደወትሮው ወር መዳረሻ ገዶት ይሆናል፣ ብዬ ‹‹ስንት መቶ?›› ስለው ‹‹ሰባት ሺህ›› አይለኝ መሰለሽ!? መስሪያ ቤቱን ሊከስ እንደሆነም ነገረኝ። ገንዘቡን ለጠበቃና ለአንዳንድ ተጨማሪ ወጪ ፈልጎ ነው። ባንክ በቆጠብኩት ሁለት ሺህ ብር ላይ ከባለቤቴ ቤተሰቦች አምስት ሺህ ብር ተበድሬ ጨምሬ ስሰጠው ‹‹ተው! ይቅርብህ! የመስሪያ ቤቱን ባለስልጣን የሾመው መንግስት ነው። መንግስት ደግሞ ከሶም ተከሶም ይረታል። ሰማይ አይታረስ ንጉስ አይከሰስን አስብ። ቃሉ ቢለወጥም ያው መንግስት ማለት ንጉስ ነው። ቀበሌ፣ ወረዳ፣ ዞን፣ ክልል፣ መስሪያ ቤቶችና መንግስት ያላቸው ልዩነት የተዋረድ ብቻ ነው›› አልኩት። ሀገሬ ሙች አልሰማኝም። እንዲያውም አልሰማ ቢለኝ በየመስሪያ ቤቶቻቸው የተሰየሙ ትንንሽ መንግስታትን ከሰው አቅላቸውን የሳቱ፣ ‹‹ቂጣቸውን በሳንጃ የተወጉ›› ዜጎችን በየዘመኑ ማየቴን፣ ገመናሽን ገልጬ ነገርኩት። አልሰማ ብሎ ፋይሉን በወረዳ ፍርድቤት ከፈተ።
በወረዳ ፍ/ቤትሽ የክስ ፋይል በከፈተ በአራት ወሩ የውሳኔውን ወረቀት አምጥቶ አሳየኝ ሀገሬ ሙች እልሻለሁ ገረመኝ! አንቺ እኮ ትገርሚያለሽ! የፍርድ ቤቱ የፍርድ ውሳኔ ከማህተሙና ከፊርማው ልዩነት በስተቀር፣ ያው የተባረረበት ደብዳቤ ግልባጭ ነው። አዘነ። ሀገሬ ሙች አዘነ። የፍትህ መዶሻሸ ያረፈበትን አናቱን ቀና አድርጎ መመልከት አቃተው።
ታከለ ግን የዋዛ ዜጋ አይደለም። ‹‹እውነትና ንጋት እያደር ይጠራል››ን እየተረተ ይግባኝ አለ። ይኽው ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሰው ሰርቶ በየወሩ ደመወዝ ሲቀበል፣ እሱ በየደረጃው በሚገኙ ፍርድ ቤቶች፣ የተባረረበትን ደብዳቤ እያፀደቀ ይመጣል።
እና ታከለ ምን ተመኘ መሰለሽ! ሀገሬ ሙች እንደገመናሽ ዝግናኔ የግል ፍርድ ቤት ቢመኝ አይፈረድበትም። አንድ እሁድ ቀን አንድ ካፌ በረንዳ ላይ ተቀምጠን ማኪያቶ ስንጠጣ፣ ከመንገዱ ባሻገር ያለውን የግል ሆስፒታል እየተመለከተ ‹‹በህይወት ዘመኔ ማየት የምመኘው ምን እንደሆነ ታውቃለህ?›› አለኝ። ‹‹ምን›› አልኩት፤ ቁብ አልሰጠሁትም። ‹‹እዚያ ህንፃ አናት ላይ በግል ሆስፒታሉ ስያሜ ምትክ ‹‹ብርሃን ከፍተኛ የግል ፍርድ ቤት፣ መለያችን ይግባኝ አልባ ፍርዳችን ነው!›› የሚል ተጽፎ ማየት። ሀገሬ ሙች አያስቅም! ደግሞ ሰው እንጂ ሀገር ሲስቅም ሲያለቅስም አያምርበትም።
እውነቱን እኮ ነው! በመንግስት ፍርድ ቤት መንግስትን መርታት ካልተቻለ፣ ለምን በግል ፍርድ ቤት አይሞከርም። በቃ ሀገሬ አንቺም የፍትህ ገመናሽን መክላት ካማረሽ፣ በቃ የግል ፍርድ ቤት ክፈቺ። እና የመንግስት ፍ/ቤቶች በዜጎችሽ መካከል ያለን ክስ ይመልከቱ። በማንኛውም ሁኔታ በመንግስትና በዜጋ መካከል ያለን ክስ ደግሞ በግል ፍርድ ቤት እንዲታይ አድርጊ። ያኔ የዜጎችሽ አናት መንግስት ለዳኞችሽ ባስጨበጣቸው መዶሻ አይነደልም። ዜጎችሽ ቀና ብለው ይሄዳሉ፤ ስለፍትህ ስርአትሽም መልካሙን አብዝተው ይናገራሉ። ከሁሉም በላይ ደግሞ አንቺ ደስ ይልሻል። አንቺ ደስ ሲልሽ ደግሞ እኛም መልሶ ደስ ይለናል።
ስለፍትህ ገመናሽ ስናገር የሰሙ አንዳንድ ዜጎችሽ፣ ‹‹እንዴት ሰው፣ ከሰው ገመና አልፎ የሀገርን ገመና አንድ — ሁለት — እያለ ያብጠለጥላል!›› እያሉ ያብጠለጥሉኛል። እኔ ምን ተዳዬ! ሀገሬ አንቺ ራስሽ ገመናሽን መች ሸፈንሽውና እኔ እኮነናለሁ? እንዴ! የምር እኮ ነው የምልሽ! ገመናሽን እንደጋለሞታ ደጃፍ ገልጠሽዋል እኮ! አንቺ ራስሽ አይደለሽ እንዴ ተቃዋሚ፣ አሸባሪ፣ አክራሪ ብለሽ ዜጎችሽን ባሰርሽ ማግስት አኬልዳማ፣ ጀሀዳዊ ሐረካት– ምናምን የሚል ፊልም እየሰራሽ የፍትህ – ገመናሽን ቲቪ ያስገባሽው! እውነት ሀገሬ ያሳፍራል።
ለዚህ እኮ ነው መንግስት የገባበት ክስ የዝሆንና የጥንቸል ፍልሚያ ነው የምልሽ። ያውም ሮጣ የማታመልጥ እግርዋ የተሰበረ ጥንቸል! ሲጀመር ለመንግስት ዝሆንነትን ሰጥተሻል። ጠመንጃ አለው፤ እስር ቤት አለው፤ ቲቪ አለው፤ ራዲዮ አለው፤ ዳኛ አለው፤ አቃቤ ህግ አለው። ይህ ሁሉ ካለኝ ደግሞ እኔም ብሆን፣ ዝሆን መሆን አያቅተኝም። ተቃዋሚ፣ ሽብርተኛ፣ አክራሪ ተብሎ የተመረጠው ደግሞ ጥንቸል ነው። ጥንቸል ከዝሆን ቢፋለም እድሉ አንድ ነው- ሮጦ ማምለጥ። አንቺ ግን ሀገሬ! ጥንቸሎችሽ በፍትህ ስርአትሽ ሮጠው ነፃ የሚወጡበት የመርፌ ቀዳዳ የምታህል ቀዳዳ እንኳን እንዳትኖር፤ ክሳቸው እንኳን ወጉ ተነቦላቸው የእምነት – ክህደት ቃላቸው ሳይሰማ፣ እንዴት እንዳከረሩ፣ እንዴት እንዳሸበሩ ፊልም ሰርተሽ በቲቪ ትለቂዋለሽ። በፍትህ አደባባይ ሮጠው እንዳያመልጡ የጥንቸሎቹን እግር ስብርብር አደርገሽ ማለት ያኔ ነው! .. ኧረ በእውነት ይዘገንናል! አባቶቻቸው ተጠርጥረው ከተከሰሱበት ወንጀል ነፃ የሚወጡበትን ቀን የሚናፍቁ ልጆችን … እናቶቻቸውን.. ጎረቤቶቻቸውን… አስቢ እስቲ! አንቺ በእነሱ ቦታ ብትሆኚና ፍትህን ያስከብርልኛል ያልሽው መንግስት በተጠረጠሩብሽ ላይ፣ እንደዚያ ያለ ፊልም እያቀረበ የፍትህን ጽንስ ለውርጃ ሲዳርግ ብትመለከቺ ምን ትያለሽ! ምንስ ታደርጊያለሽ! ዳሩ አንቺ ሀገር እንጂ ዜጋ አይደለሽም። ዜጋስ ብትሆኚ እግሮችዋ የተሰበሩ ጥንቸል ሆነሽ መታገል ከማይሰለቸው ዝሆን ፊት ብትቆሚ እጣሽ ምንድነው? አቦ ሀገሬ ተይኝ! ገልጠው የማይጨርሱት ገመና አድሎሻል

ጥልያን በመድፍ በመትረየስ በአውሮፕላን ሊገድለው ያልቻለውን ጀግና በቅናት የተነሳሱ መቀኞች የሸረቡት ገመድ ገደለው

በላይ ዘለቀ ጀግና ብቻ አልነበረም፡፡ ባንዳነትን አድረባይነትን ሎሌነትን አጥብቆ ይጠላም እንደነበር ከዚህ ታሪኩ መረዳት እንችላለን፡፡ “….በላይ ዘለቀ ተኩሶ አይስትም ::ፍጥነቱ ደሞ ሲደግንና ሲተኩስ እኩል ነው ::ውጊያ ሊጀምር ሲል "እኔ ሳልተኩስ እንዳትተኩሱ " ብሎ ያዛል ::አንዳንድ ጊዜ በውጊያ ሰአት "እርስዎ እዚህ ይቆዩን " ሲሉት "ምን ?" ይላል ቁጣ እየጀመረው ::"እርስዎ ከወደቁ መሪ የለንም " ሲሉት "ወይድ ! እኔ አሮጌ ነፍጠኛ ነኝ ::"ይልና ግንባር ይጋፈጣል :: በላይ ዘለቀ እራሱ ሲዋጋ "ገምባው " ይተበባለው ጥሩንባው ይነፋል ::"ገምባው "ባንዳን ያስበረግጋል ::ጥልያንን ያብረከርካል ::
በላይ ዘለቀ የዘመኑን አስተሳሰብ በማወቁ ህዝቡን ለማስተባበር "ትልቅ ሰው " ማስፈለጉን በመገንዘቡ እሱ እራሱ ግን ተራ ሰው በመሆኑ የንጉስ ተክለሀይማኖት ሀረግ ለሆኑት ለልጅ ሀይሉ በለው ደብዳቤ ጻፈላቸው :: የደብዳቤው ሀሳብ ባጭሩ "ህዝቡን ለማስተባበር እርስዎ የበላይ ሆነው እነን የጎበዝ አለቃ ይሹሙኝና ጠላትን እንቋቋመው ::እኔም እዋጋለሁ ::እርስዎ ወደጦር ግንባር መድረስ አይኖርብዎትም ::" የሚል ነበር ::ደጋግሞ ደብዳቤ ጻፈላቸው ::ገጸበረከትም ላከላቸው ::...ጠመንጃ ሽጉጥ ዝናር ከነጥይቱ ሶስት መቶ ብርና ካባ :: ልጅ ሀይሉ በለው ለደብዳቤዎቹ አንድም መልስ ሳይሰቱ አንድ ቀን አንድ የትእዛዝ ደብዳቤ ላኩበት ::"ደብረወርቅ ገበያችንን ያለአግባብ ቀረጡብን ብለዋልና ከንግዲህ ቆቅ የሰገረ ወፍ የበረረ እንዳይደርስባቸው ::የተወሰደባቸውም ቀረጥ እንዲመለስላቸው ::"
በላይ ዘለቀ ተናደደ ::አብረውት የነበሩትን "ጎበዝ እግዚአብሄር የወለደው ሰው አለ ?" ሲል ጠየቀ :: "እግዚአብሄር ይፈጥራል እንጂ አይወልድም " አሉት :: "ንጉስስ ?" "ንጉስም እግዚአብሄር ይቀባዋል እንጂ አይወልድም ::ይፈጥረዋል እንደሌላሰው " "እኔንም ፈጥሮኛል ::ሊቀባኝ አይችልም ?" "የሱ ሀይል ካደረብዎ የፈለጉትን ማድረግ ይችላሉ ::" "እንግዲህ ከዛሬ ጀምሮ ለማንም አልታጠቅም ::" ተመስገን ፈንታ የበላይ ዘለቀ የቅርብ ጉዋደኛው ነበር ::አንድ ቀን ከጠላት በፊት ተመስገን ፈንታ በላይ ዘለቀን "ሸዋ ሄደን ለትልቅ ሰው እንደር ::እንሾማለን ;እንሸለማለን "አለው :: "እኔ ሰው ሆኜ ለሰው አላድርም "አለ በላይ ዘለቀ :: "ባንተ ተኩስ ;ባንተ ወኔ ;ባንዳፍታ ትሾማለኽ :: "ጀግንነት እደጃችን ድረስ ይመጣ እንደሆነ ማን ያውቃል ?" አለው በላይ ዘለቀ ::አመታት አለፉ ::
ሞረድ እጀ ጠባብ ካስመራ እሚመጣ አፈ ሾሌ ሱሪና ተመሳሳይ ኮኮት ጥንግ ድርብ ጥበብ ኩታ በቅሎ እንደተጫነች ጠመንጃ ከነሙሉ ዝናር ጥይት ...በላይ ዘለቀ ይህንን ሁሉ አዘጋጀና ተመስገን ፈንታን ጠርቶ ; "ያ የጌታ አዳር ሄደን እንሸለማለን ያልከው ይኸውና "ብሎ ሸለመው ::በአርበኝነት ዘመን ጉዋደኛሞቹ አልተለያዩም :: በላይ ዘለቀ መጀመርያ "ራስ " ብሎ የሾመው ተመስገን ፈንታን ነበር :: "እኔንስ ራስ አልከኝ ::አንተ ማን ልትባል ነው ?" አለው ተመስገን ፈንታ :: "እኔንማ እናቴ አንደዜ በላይ ብላኛለች " አለ በላይ ዘለቀ ::” ……….
የበላይ መጨረሻም ይህ ሆነ፡፡ ንጉስ ሹም ሽር አደረጉ ::በላይ ዘለቀ ከወንድሞቹ ጋር ሆኖ በሁዋላም ከአገሬው ጋር ሆኖ ጠላትን ተዋግቶ ነጻ ያወጣው ጠቅላይ ግዛት ለራስ ሀይሉ ተሰጠ :: በላይ ዘለቀ ወዳዲሳባ ተጠርቶ ደጃዝማች ተብሎ የቢቸና አውራጃ ገዥ ሆኖ ተሾመ :: የቢቸና አውራዣ ገዥ ሆኖም ሊሰራ አልቻለም ::ከደብረ ማርቆስ ትእዛዝ እየመጣ ወረዳዎቹ ሁሉ ቀድሞ ባንዳ የነበሩ ሰዎች ተሾሙባቸው ::ብስጭት በዛበት በላይ ዘለቀ :: "ሊወጋን ነው ....እምቢ አለ ..."እያሉ ማስወራት ጀመሩ :: በቂ ካስወሩ በሁዋላ ከራያና አዘቦ ጦር አስዘመቱበት :: (ጎጃመማ በላይ ዘለቀን ወይ ይወደዋል ወይ ይፈራዋል :: ) በላይ ዘለቀና ወንድሞቹ ከጥቂት ታማኝ ተከታዮቹ ጋር ሆነው ወደ ሳማ አምባ ሸሹ ::በላይ ዘለቀ ሸፈተ ተባለ :: ሳማ አምባ ያለ ሁለት በር የላትም ሁለቱንም በር ይዘው ሀያ አምስት ቀን ሌትና ቀን ተዋጉ :: "ምረነዋል ልቀቁት ይምጣ "የሚል መልእክት ከንጉሱ መጣ :: ከሳማ አምባ ከወረዱ በሁዋላ ተከበቡና መሳሪያቸውን ተነጥቀው እንደ እስረኞች ወደ አዲስ አበባ ተወሰዱ :: በላይ ዘለቀ ሞት ተፈረደበት ::ንጉሱ "ምህረት " አደረጉለትና ቅጣቱ ወደ እስራት ተለወጠለት ::
መስከረም 1936 አ .ም በላይ ዘለቀና ወንድሞቹ በያገሩ ተበትነው ታሰሩ :: በላይ ዘለቀና ወንድሙ እጅጉ ዘለቀ ወሊሶ በበቀለ ወያ ጠባቂነት ታሰሩ :: የበላይ ዘለቀ ምቀኖች አሁንም አላረፉለትም ::በላይ ዘለቀ ከዳ ;አመለጠ ጠፋ እየተባለ ይወራ ጀመር ::በቀለ ወያ ተያዘና "ምን ቢሰጥህ ነው የለቀከው ?"ተባለ ::"እረ እኔ አልለቀኩትም አለ :::: በላይ ዘለቀና እጅጉ ዘለቀን ወደ አዲስ አበባ አመጡዋቸውና ከአንድ ሌላ ሰው ጋር አሰሩዋቸው :.ያ ሰው እናምልጥ እያለ እነ በላይ ዘለቀን ይጎተጉታቸው ጀመር :: አንድ ቀን "ጠባቂዎቻችንን የኛ ወዳጆች ገዝተዋቸዋልና እናምልጥ ::በንዲህ ያለ ስፍራ እነ እገሌ መኪና ይዘው እየጠበቁን ናቸው ::"አል :: "ወንድሞቸ በየቦታው ተበታትነው ታስረው እኔ ማምለጥ ምን ያረግልኛል ?" አለ በላይ ዘለቀ :: "ፈራህ እንዴ በላይ ዘለቀ ?"አለው :: "እኔ የዘለቀ ልጅ !" በላይ ዘለቀ ወንድሙን ላከው መኪናው እተባለበት ስፍራ መኖሩን ለማረጋገጥ ::ወንድምየው በተባለበት ስፍራ መኪና አየ ::እስረኞቹና ጠባቂዎቻቸው አብረው አመለጡ ::እመኪናው ቦታ ሲደርሱ መኪናው የለም ::እንግሊዝም የለም :: ጠባቂዎቻቸው ከዚያ ሮጠው አጠገባቸው ከነበረው ጫካ ገቡና ደጋግመው ተኮሱ ::ምልክት ነው :: በላይ ዘለቀ እጠላቶቹ ወጥመድ ውስጥ መግባቱን አወቀ :: በላይ ዘለቀና እጅጉ ዘለቀ ከዚያ እሮጠው አመለጡ :: ሰላሌ ደርሰው በቅሎ ለመከራየት ሲነጋገሩ ተከበቡ :: በላይ ዘለቀ በጦር ፍርድ ቤት ሞት ተፈረደበት ::ንጉሱ ፍርዱን አጸደቁት :: ጥር 1937:.በላይ ዘለቀ በስቅላት ሞተ ::እድሜው ሰላሳ አምስት አመት ነበር ::
ጥልያንን በመድፍ በመትረየስ በአውሮፕላን ሊገድለው ያልቻለውን ጀግና በቅናት የተነሳሱ መቀኞች የሸረቡት ገመድ ገደለው ::ፊታውራሪ ተሻለ አለሙ ሰላሳ አምስት አመት ታስረው በለውጡ ተፈቱ::መልኩን ፊታውራሪ ተሻለ አለሙ እንዲህ ብለው ይገልሱታል :: "አፍንጫው ሰተት ብሎ ወርዶ ቅጠሉ ነፋ ነፋ ይላል ::ከንፈሩ ከበድ ይላል ::ጠጉሩ ክርክም ጎፈሬ ጺሙ ሙሉ ለስላሳ ረጅም ጣቱ መልካም ወተት የተነከረ ነው የሚመስለው ጣቱ ::እግረ ቀጭን ::"…………..”
ዛሬም እንደዚህ ነው…. ስንት አድርባዮችና አሰመሳዮች አለን? ኑሮአችንን በሌሎች ህልውና ላይ የመሰረትን? የአፋኝ ሥርዐት ሎሌ በመሆን የወንድሞቻችንን ደም ከንቱ ያደረግን…..?

Mar 26, 2013

ከቤንሻንጉል ጉሙዝ የተፈናቀሉ 60 የአማራ ተወላጆችን ይዞ ሲጓዝ የነበረ አይሱዙ መኪና ተገልብጦ 59 ሰዎች ሞቱ


መጋቢት ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም 

ኢሳት ዜና:-ከአካባቢው ተፈናቃይ አርሶ አደሮች ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው አደጋው የተፈጠረው፣ ሰዎችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረው መኪና ትክሻ በምትባል ቀበሌ ውስጥ ጀዴሳ በሚባል ወንዝ ውስጥ ገብቶ ነው።
ከትናንት ወዲያ በተፈጠረው አሰቃቂ አደጋ ለሞቱት ሰዎች የደረሰላቸው ሰው አለመኖሩን ለደህንነታቸው በመስጋት ስማቸው እንዳይገልጽ የፈለጉ ተፈናቃይ አርሶደሮች ተናግረዋል።
ከሞቱት መካከል ህጻናትና ሴቶችም ይገኙበታል። በአደጋው ዙሪያ የክልሉን ባለስልጣናት ለማነጋገር ተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም አልተሳካልንም።
በተመሳሳይ ዜናም በዛሬው እለት በርካታ አርሶ አደሮች በክልሉ ልዩ ሚሊሺያ ጥቃት እንደደረሰባቸው ተናግረዋል።
የክልሉ ባለስልጣናት የሚፈናቀሉት ሰዎች በህገወጥ መንገድ ወደ ክልሉ የገቡ ናቸው ሲሉ ለአዲስ አድማስ መናገራቸው ይታወሳል።
የዜጐች ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብትን በተለከተ አስተያየታቸውን የሰቱት የሕግ ባለሞያ አቶ ግዛው ለገሠ የሕገ-መንግሥቱ አንቀፅ 32 “የመዘዋወር ነፃነት” በሚል ርእስ ስር ‹‹ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ወይም በሕጋዊ መንገድ አገሪቱ ውስጥ የሚገኝ የውጭ ዜጋ፤ በመረጠው የአገሪቱ አካባቢ የመኖርና የመኖሪያ ቦታ የመመስረት እንዲሁም በፈለገው ጊዜ ከአገር የመውጣት መብት እንዳለው መደንገጉን ለጋዜጣው ገልጸዋል።

የእስልምና ምክር ቤት ዋና ጸሀፊ የነበሩት ግለሰብ ብአዴን ኮትኩቶ ያሳደጋቸው ሰው መሆናቸው ታወቀ

የእስልምና ምክር ቤት ዋና ጸሀፊ የነበሩት ግለሰብ ብአዴን ኮትኩቶ ያሳደጋቸው ሰው መሆናቸው ታወቀ
መጋቢት ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም 
ኢሳት ዜና:-በቅርቡ ከተካሄደው ምርጫ በፊት የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ዋና ጸሀፊ የነበሩት ሀጂ መሁመድ ሲራጅ ሙሀመድ ኑር አባታቸው ዋግ ውስጥ ነባር የብአዴን ታጋይ የነበሩ ሲሆን፣ የአቶ ተፈራ ዋልዋ እና የአቶ አዲሱ ለገሰ የቅርብ ሰው እንደነበሩ ከብአዴን ምንጮች የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ግለሰቡ በአወልያ የተጀመረው ተቃውሞ እንዲኮላሽ ከመንግስት ከፍተኛ ተልእኮ በመያዝ ሲንቀሳቀሱ የነበሩና አሁንም የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ልማት ኤጀንሲ የተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ለመንግስት ምክር እየሰጡ የሚገኙ ናቸው።
የግለሰቡ ታሪክ እንደሚያስረዳው ታጋይ አባታቸው ሲራህ መሀመድ ኑር እንደሞቱ ወጣቱ ሲራጅ በአቶ አዲሱ አማካኝት የአማራ ክልል ወጣቶች ማህበርን እንዲያደራጁ ተመርጠው ማህበሩ እንዲመሰረት ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። በዚህ አስተዋጽኦቸውም፣ ምንም አይነት በቂ የእስልምና እምነት ትምህርት ሳይኖራቸው የአማራ ክልል እስልምና ጉባኤ ሃላፊ ተብለው በመንግስት ከተሾሙ በሁዋላ ለተወሰነ ጊዜ በክልሉ ውስጥ እንቅስቃሴ አድርገዋል።
በ1997 ዓም ግለሰቡ ወደ ፌደራል ተዛውረው መጠነኛ የእስልምና ሀይማኖት ትምህርት እንዲቀስሙ ከተደረጉ በሁዋላ የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ዋና ጸሀፊ በመሆን ከፍተኛ የፖለቲካ ስራ ሲሰሩ ቆይተዋል።
ሀጂ ሙሀመድ በአማራ ክልል ዋና ከተማ ባህርዳር የክልሉን የእስልምና ምክር ቤት በከተማዋ መሀል አደባባይ ላይ በአለ አራት ፎቅ ህንጻ እያሰሩ ሳለ፣ ከህንጻው ስራ ጋር በተያያዘ ገንዘብ ማጉደላቸው በመረጋገጡ ፣ የህንጻው ስራ እስካሁን ካለመጠናቀቁም በላይ ግለሰቡ እንዳይጠየቁ ተደርጓል።
በሰቆጣ ለእናታቸው እጅግ ዘመናዊ ህንጻ የገነቡት ሀጂ ሙሀመድ፣ ሶስት የንግድ መኪኖችን ገዝተው በንግድ ስራ ላይ ከመሰማራታቸው በላይ፣ በባህርዳር፣ በአዲስ አበባ እና በሰቆጣ የንግድ ቤቶችንና የመኖሪያ ቤቶችን በራሳቸውና በወንድሞቻቸው ስም በመገንባት በአጭር ጊዜ ውስጥ ከድህነት ወደ ሀብታሞች ጎራ ለመቀላቀል ችለዋል።
በቅርቡ በተደረገው የመጅሊስ ምርጫ ስልጣናቸውን ያስረከቡት የ40 አመቱ ሀጂ ሙሀመድ፣ አሁን ደግሞ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ልማት ኤጀንሲ የተባለ ድርጅት ከፍተው መንግስትን እያማከሩ ነው።
በእስር ላይ የሚገኙ የሙስሊም መሪዎች እና ድምጻችን ይሰማ በማለት ዘወትር አርብ ተቃውሞ የሚያሰሙ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ምክር ቤቱ ነጻ አይደለም በማለት ጥያቄ ማቅረባቸው ትክክልና በማስረጃ የተደገፈ መሆኑን የብአዴን ምንጮች የዋና ጸሀፊውን ማንነት በማስረጃ በማስደፍ እንደ ማሳያ አቅርበዋል። በቅርቡ የተተኩት የመጅሊስ አባላትም እንዲሁ የኢህአዴግ ቀንደኛ ደጋፊና አባላት መሆናቸውን የደረሰን መረጃ አያይዞ ገልጾአል።
አቶ ተፈራ ዋልዋ ብዙውን ጊዜ አቶ አዲሱ ለገሰ ደግሞ አልፎ አልፎ በህይወት ያሉት የሀጅ መሀመድ ሲራጅን እናት የታጋይ ሲራጅ ሙሀመድ ኑርን ባለቤት እየሄዱ እንደሚጠየቁቸው ታውቋል።
በጉዳዩ ዙሪያ የሀጂ አል ሙሀመድ ሲራጅን አስተያየት ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

Mar 21, 2013

በደም እንደመጣን በደም ነዉ የምንወጣዉ!!! ህዉሃት





የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመራጮችን ምዝገባ አካሂዶና ለተፎካካሪዎችም ምልክት ሰጥቶ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ በቅርቡም ተፎካካሪዎች ፖሊሲያቸውንና ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለማቸውን ለሕዝብ የሚያስተዋውቁበት የሰዓት ድልድል አድርጎ የምርጫ ቅስቀሳ ተጀምሯል፡፡

ስሜት እና ቁጥር ለየቅል?
ወ/ሮ ዘርዬ በለጠ ዕድሜያቸው 39 ሲሆን የቤት እመቤት ናቸው፡፡ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ይኖራሉ፡፡ ሕዝቡም ሆነ መንግሥት ለምርጫው የሰጡት ትኩረት ይህን ያህል አይደለም ይላሉ፡፡ ‹‹ይህ ምርጫ ምንም ይሁን ምን በብዙኅኑ ዘንድ በውል የታወቀ አይመስለኝም፡፡ ለማንኛውም ምረጡ ተብለን እስከተጠየቅን ድረስ መምረጥ ተገቢ ነው ብዬ ስለማስብ እመርጣለሁ፡፡ ማንን ልምረጥ? ማን ምን ይሁን? ማን ከማን ጋር ይፎካከር? ግን ምንም መረጃ የለኝም፡፡ እኔም ፈልጌ አላጣራሁም፤›› ይላሉ፡፡

ከአንድ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ ባህሪያት መካከል አንዱ የተመዝጋቢዎችን ቁጥር (turn out) ማየት ነው፡፡ ዕድሜያቸው ለምርጫ ከደረሱ ዜጎች እስከ 70 በመቶ ወጥተው ድምፃቸውን ከሰጡ የሕዝቡ ተሳትፎ ከፍተኛ መሆኑን አመላካች ነው፡፡ ሕዝቡም ለሚሰጠው ድምፅ ከፍተኛ ዋጋ መስጠቱን የሚያመላክተው የሚሰጠው ድምፅም በትክክል ይቆጠራል፣ ለውጥም ያመጣል በሚል እምነት የታጀበ ነው፡፡

የተመዝጋቢው ቁጥር በተለይ ደግሞ ተመዝግቦ የምርጫ ካርድ ወስዶ በምርጫው ዕለት ድምፅ የሚሰጠው ቁጥር ማነስና መብዛት ሕዝቡ በሥርዓቱ ላይ ያለውን አመኔታም አመላካች ነው፡፡ ድምፄ በትክክል አይቆጠርም የሚል ግምትና እምነት ካደረበት የመራጭ ካርድም ወስዶ ድምፁን መስጠት እንደ ከንቱ ልፋት ስለሚቆጥረው ሒደቱን ከቁብ አይቆጥረውም፤ አይመዘገብም፤ ከተመዘገበም ድምፅ ላይሰጥ ይችላል፡፡ ድምፄ ይጭበረበራል በሚል፡፡ ወይም ደግሞ እንደ ወ/ሮ ዘርዬ ለምን እንደሚመርጥም መረጃ የለውም፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ2005 ዓ.ም. በሚካሄደው የአካባቢ፣ የአዲስ አበባና የድሬዳዋ መስተዳደር ምክር ቤቶች ምርጫ ከታኅሳስ 22 አስከ ጥር 21 2005 ዓ.ም.፣ እንዲሁም ደግሞ ጊዜውን በማራዘም ጥር 24 እና 25 ቀን 2005 ዓ.ም. ባካሄደው የምዝገባ ወቅት ቀድሞ ያስቀመጠው ግምትና ተመዘገበ ያለውን የሕዝብ ቁጥር አነፃፅሮ አስቀምጧል፡፡ ቦርዱ ከማዕከላዊ ስታትስቲክስ ባገኘው መረጃ መሠረት፣ በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር 86 ሚሊዮን የሚገመት ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ ዕድሜው ለመራጭነት የደረሰው 40 በመቶ (34.5 ሚሊዮን) ነው፡፡ ከእነዚህ መካከል ተመዝግበው ካርድ ይወስዳሉ ብሎ የገመተው 83 በመቶ ወይም 28.5 ሚሊዮን ሕዝብ እንደነበር በመረጃ ሰንጠረዡ አስፍሯል፡፡

ቦርዱ ባካሄደው ምዝገባ 30.6 ሚሊዮን ሕዝብ የምርጫ ካርድ የወሰደ ሲሆን፣ ይኼም በቦርዱ ቀድም ሲል ከተገመተው 83 በመቶ አልፎ 88.93 በመቶ ደርሷል፡፡

ካለፉት ምርጫዎች ጋር  ሲነፃፀር ዘንድሮ ምርጫ ቦርድ ይፋ ያደረገው የመራጮች ቁጥር እጅግ ከፍተኛ የሚባል ነው፡፡ ዋናው ጉዳይ ምርጫ ቦርድ የመዘገበው ቁጥር እውነት ነው ወይ አይደለም በማለት በርካቶች የሚያነሱት ጥያቄ ነው፡፡ ይህንን ጥያቄ ለማንሳት ምክንያት የሚሆኑ ሁለት መሠረታዊ ነገሮችን ማንሳት ይቻላል፡፡ አንደኛው ምርጫው ሊካሄድ የቀረው ጊዜ ከአንድ ወር የማይበልጥ ቢሆንም፣ በሕዝቡ ውስጥ ‹‹ምርጫ ምርጫ›› የሚሸት መንፈስ አለመኖሩ ነው፡፡ በማኅበራዊ ሚዲያ (ፌስቡክም ሆነ ትዊተር) በርካታ ኢትዮጵያዊያን ስለ ኬንያ ምርጫ በርካታ ነገሮች ሲጽፉና ሲወያዩ እየተስተዋለ ነው፡፡ ከዚህ በፊት የተካሄደው የኬንያ ምርጫ ለበርካታ ኬንያውያን ሞት ምክንያት የነበረ ሲሆን፣ በንፅፅር የአሁኑ ሰላማዊና ብዙም ትችት ያልቀረበበት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋን አሸንፈው ቀጣዩ የኬንያ ፕሬዚዳንት የሚሆኑት ኡሁሩ ኬንያታ ናቸው፡፡ ስለኢትዮጵያ መጪው ምርጫ አንስቶ የሚወያይ ግን እስከዚህም ነው፡፡

በኢትዮጵያ በቅርቡ የሚካሄደው ምርጫ የመንግሥት ለውጥ የሚደረግበትና አዲስ መሪ ለማየት የሚጓጓበት ባይሆንም፣ የዲሞክራሲያዊ ምርጫ ዋና መገለጫ የሚሆነው የሕዝብ ተሳትፎ ግን ከዋናው ምርጫም የበለጠ ክብደት ሊሰጠው በተገባ ነበር፡፡ ሕዝቡ ከክፍለ ከተማ ጀምሮ እስከ ቀበሌ ድረስ ያሉ የቅርብ አስተዳዳሪዎቹን በቀጥታ የሚመርጥበት በመሆኑ፣ የሕዝቡ ዋና ቅሬታዎች የሆኑት የፍትሕና የመልካም አስተዳደር ችግሮች የሚታዩበት የመንግሥት አስተዳደር እርከንም ነው፡፡

መንግሥት፣ ኢሕአዴግና ቦርዱ ሕዝቡ የምርጫውን አስፈላጊነት ሙሉ ግንዛቤ አግኝቶ ተመዝግቦ ከሚቀርቡለት ዕጩዎች መካከል ለመምረጥ መዘጋጀቱን እየተናገሩ ነው፡፡ አንድ ማስረጃቸውም፣ ካርድ የወሰደው የሕዝብ ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን በመጥቀስ ነው፡፡ ተመዘገበ በሚባለው መራጭ ቁጥር ላይ ጥርጣሬ ያላቸው ሰዎች ግን ሕዝቡ ውስጥ ስለምርጫው ያለው ስሜት የሞተ መሆኑን ይናገራሉ፡፡

ከዚህም ጋር በተያያዘ ሌላ ጥርጣሬ ያላቸው አሉ፡፡ በተደጋጋሚ በገለልተኝነቱ ላይ ጥያቄ የሚነሳበት ምርጫ ቦርድ፣ መንግሥትን (ኢሕአዴግን) ለማስደሰት ቁጥሩን ከፍ አድርጎ አለመሆኑን ምንም ማረጋገጫ የለም ይላሉ፡፡ ሕዝቡ በምርጫ ሒደት ተስፋ የቆረጠ የሚመስል ሁኔታ እየተስተዋለበት ሲሆን፣ በምርጫ ወቅት የቀበሌ ሠራተኞች (ካድሬዎች) ቤት ለቤት ባደረጉት ቅስቀሳ በተፅዕኖና መንግሥትን በመፍራት ካርድ የወሰደው ይበዛል የሚል ግምት ያላቸውም አሉ፡፡ የምርጫ ቦርድ መዘገብኩት በሚለው ተመዝጋቢ ቁጥር ብዛት ተዓማኒነት ላይ ጥርጣሬ የሌላቸው ጥቂቶች ይመስላሉ፡፡

ያለ ተወዳዳሪ ምርጫ
የምርጫው ወሬ በተጀመረ ሰሞን ምርጫ ምርጫ የሚሸቱ ዜናዎችና መግለጫዎች መሰማት ጀምረው ነበር፡፡ በተለይ ምርጫ ቦርድ የምርጫው የጊዜ ሰሌዳ ላይ ለመነጋገር በሕጋዊ መንገድ ተመዝግበው የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ለማነጋገር በአዳማ በጠራው ስብሰባ የተነሳ ነበር፡፡

በወቅቱ ‹‹የአገሪቱ የፖለቲካ ምኅዳር የሚያሠራ አይደለም›› በሚል ከምርጫው ፕሮግራም በፊት በእዚህ ጉዳይ ላይ ከኢሕአዴግ ጋር ቁጭ ብለው ለመነጋገር ጥያቄ ያቀረቡ ከ40 በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች ድምፃቸውን አሰምተው ነበር፡፡ ከእነዚህም መካከል በተለይ ‹‹33ቱ›› የሚባሉት የጋራ ጊዜያዊ ኮሚቴ በማቋቋም ቅሬታቸውን አግባብ ባለው መንገድ ለምርጫ ቦርድና ለሚመለከተው የመንግሥት አካል አቅርበው ሰሚ አለማግኘታቸውን በተደጋጋሚ ተናግረዋል፡፡

ዕጩዎች የምርጫ ምልክት የሚወስዱበት ቀነ ገደብ ቢጠናቀቅም፣ ፓርቲዎቹ ከምርጫ ውድድር ውጪ ሆነዋል፡፡ በዚህ ቡድን ውስጥ የተሰባሰቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች መድረክንና መኢአድን ጨምሮ ዋና የሚባሉ የተቃዋሚ ስብስቦች የሚገኙበት ነው፡፡ መንግሥት 29 የፖለቲካ ፓርቲዎች የመወዳደሪያ ምልክት ወስደው ለዕጩነት መዘጋጀታቸውን ቢገልጽም፣ ከዚህ የሚበልጥ ቁጥርና ተቀባይነት ያላቸው ተቃዋሚዎች ወደ ሒደቱ ለመምጣት ምንም ጥረት አላደረጉም፡፡ የኢትዮጵያውያን ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) አንድ ዕጩ በማቅረብ በአዲስ አበባ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ለመወዳደር የወሰነው በምርጫው ሒደት አምኖበት እንዳልሆነ በቅርቡ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል፡፡ ከምርጫው ሒደቱ ራሱን ለማግለል የወሰነው፣ እንደ ፓርቲ ለሦስተኛ ጊዜ ራሱን ከምርጫ ካገለለ በሚቀጥለው ምርጫ መሳተፍ ስለማይችል ነው፡፡ በመሆኑም በዚህ የሕግ ተፅዕኖ ምክንያት በሒደቱ የሚሳተፈው ኢዴፓ፣ ከምርጫው ራሱን እንዳገለለ ነው የሚታሰበው፡፡

የተቀሩት ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች አንድም በሕዝብ አይታወቁም፣ አለበለዚያም ከኢሕአዴግ አንዳንድ ጥቅማ ጥቅሞች ስለሚጠብቁ በሕዝብ ያላቸው ተቀባይነትም እስከዚህም ነው የሚሉ አሉ፡፡ በምርጫው ያላቸው ሚናም ለሕዝቡ አማራጭ ሆነው ይፎካከራሉ ሳይሆን፣ ኢሕአዴግን በሒደቱ በማጀብ ከዓለም አቀፍ ነቀፌታ መታደግ ብቻ ነው ተብለው የሚታመኑ ናቸው፡፡ በዚህም ሒሳብ አንድም የሚታወቅ ተቃዋሚ የማይወዳደርበት የአካባቢ ምርጫ፣ ያለተቃዋሚ የሚደረግ ምርጫ ነው ለማለት የሚያስደፍር ነው፡፡

የ97 ጦስ
አቶ አበራ ዘገዬ ዕድሜያቸው 56 ሲሆን የእንጨት ሥራ ባለሙያ ናቸው፡፡ ‹‹የአዲስ አበባ ምክር ቤት ምርጫ ወትሮም ቢሆን የተጋነነ ሁኔታ አይታይበትም፡፡ በእርግጥ ብሔራዊ ምርጫውም ቢሆን ከ97 ዓ.ም. በኋላ ያን ያህል አጥጋቢ አይመስለኝም፤›› በማለት ተስፋ በመቁረጥ ስሜት ይናገራሉ፡፡ ‹‹ሰሞኑን ተጀመረ የተባለውን የምረጡኝ ቅስቀሳ ግን ልብ ብዬ ሰምቼውም አላውቅም፡፡

 ይህ ደግሞ የኔ ብቻ ሳይሆን የአብዛኛው ሰው ስሜት ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም ማንም ሰው ስለጉዳዩ ሲያወራ አይታይም፡፡ በአጠቃላይ የምክር ቤትና የአካባቢ ምርጫ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ቅዝቀዝ ያለ ሁኔታ ነው ያለው፡፡ እኔ በአግባቡ በተመቸኝ ሰዓት ሄጄ ነው የምርጫ ካርዴን የወሰድኩት፡፡ የማውቃቸው ሌሎች ብዙ ሰዎች ግን ኑ ውሰዱ ተብለው እንደወሰዱ አውቃለሁ፤›› ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ ሞቅ ሞቅ ያለ ቅድመ ምርጫና የምርጫ ወቅት የታየበት ሦስተኛው አገራዊ የ97 ምርጫ ተጠቃሽ ነው፡፡ ሆኖም ምርጫውን ተከትሎ በተፈጠረው የፖለቲካ ቀውስ ኅብረት ፈጥረው ገዥውን ፓርቲ ተፈታትነው የነበሩ ተቃዋሚዎች ተበታትነዋል፡፡ በምርጫው ማግስት በፀደቁት አንዳንድ አፋኝ ሕጎች የተወሰዱ አስተዳደራዊ ዕርምጃዎች ተከትሎ በ2000 ዓ.ም. የተደረገው የአካባቢ ምርጫ ጀምሮ ነበር ኢሕአዴግ የፖለቲካ ሁኔታውንና የምርጫውን ሒደት ሙሉ ለሙሉ መቆጣጠር የቻለው፡፡

በወቅቱ እስከ አምስት ሚሊዮን አባላት የመለመለው ኢሕአዴግ፣ ለአካባቢ ምርጫ በአጠቃላይ እስከ ሦስት ሚሊዮን መቀመጫዎች እንዲቀርቡ ያደረገ ሲሆን፣ በወቅቱ ጠንካራ ከነበሩ ተቃዋሚዎች ኅብረትና ኦፌዲን ራሳቸውን ከሒደቱ ሲያገሉ፣ ኢዴፓ ለተሳትፎ ሲል ተወዳድሯል፡፡ በቅንነት የተደረገ ምርጫም አልነበረም በማለት የሚተቹ ብዙ ናቸው፡፡

ቀጥሎም በተካሄደው የ2002 ዋና ምርጫ መድረክ የተባለው የፖለቲካ ፓርቲዎች ስብስብ ሆኖ ብቅ ያለ ቢሆንም፣ ከአንድ የፓርላማ መቀመጫ ውጪ ማግኘት አልቻለም፡፡ ከምርጫው በፊት ጀምሮ የፖለቲካ ምኅዳሩ የማያፈናፍን ሆኗል በሚል የሚቀርብበትን ትችት ጆሮ ዳባ ልበስ ያለው ኢሕአዴግ፣ ሒደቱ በነበረበት ቀጥሎ ዋናዎቹ ተቃዋሚዎች ከምርጫ ውጪ ሆነው፣ ሕዝቡ በተፅዕኖ የምርጫ ካርድ የሚወስድበትና የደበዘዘ የምርጫ ሒደት የሚታይበት የአሁኑ ወቅት ላይ መደረሱን ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ተቺዎች የሚስማሙበት ነው፡፡

የብዙ አስተያየት ሰጪዎች ሥጋት የፖለቲካ ምኅዳሩ አሁን ባለው ሁኔታ የሚቀጥል ከሆነ ሕዝቡም ሆነ ዋነኛ ተቃዋሚዎች በምርጫ መንግሥት መለወጥ አይቻልም የሚል ሙሉ ሙሉ ተስፋ መቁረጥ እንዳያስከትል ነው፡፡ በዚህም ምክንያት በሰላማዊ መንገድ ኢሕአዴግን መቃወምና መታገል አይቻልም የሚል ስሜት ሊፈጠር እንደሚችል ይታመናል፡፡ ኢሕአዴግ ምርጫን ሥልጣኑን ለማራዘም የሚጠቀምበት ስልት ነው በሚል ነፍጥ የሚያነሱ አማፂዎች የበለጠ ድጋፍ እያገኙ ሊሄዱ ይችላሉ የሚል ሥጋትም አለ፡፡

የትግራይ ህዝብ ስማ!!


ሰሞኑን በውዴታም ይሁን በግዴታ በመቀሌ እጅግ ከፍተኛ የሚባል ቁጥር ያላቸው የትግራይ ተወላጆች ሲጨፍሩ፣ ሲዘሉ፣ ከበሮ እየመቱ የባህላቸውን ዘፈንና ውዝዋዜ ሲያወርዱ አይተናል። ምክንያቱ በግልጽ ባይነገርም ሲደበቅ የነበረው የህወሃት ሃብትና ንብረት ውጤት የሆኑ፣ በልዩ የመንግስት ድጋፍ የተከናወኑ ግዙፍ ተቋሞች በጎዳና ለህዝብ ሲቀርቡም ተስተውሏል። ልማቱ መልካም ነው። ደስ ይለናል። ምንም ተቃውሞ የለንም። ግን መልዕክት አለን።
ለማን?
ምሬትን፣ ጭቆናና መንገፍገፍ ሲበዛ በፍቃደኛነት በቦንብ ላይ እንደሚያስሮጥ ለሚያውቀው የትግራይ ህዝብ!! የትግራይ ህዝብ ስማ!!
ሰሞኑን ይፋ የሆነው የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም ሪፖርት የትግራይ ክልል በትምህርት፣ በኤሌክትሪክ፣ በመንገድ፣ በእርሻ፣ በደን፣ በኢንዱስትሪ፣ በጤና፣ ወዘተ ከሌሎች ክልሎች ሁሉ ርቃ መሄዷን ይፋ አድርጓል። በዚህም ደስ ይለናል። አይከፋንም። ከዚህ በላይ እንዲሆን እንመኛለን። ነገር ግን አንድ መልዕክት አለን።
ለማን?
አሁንም ለትግራይ ህዝብ!!
ሓውዜን የትግራይ ወጣቶች ለትግል ግልብጥ ብለው እንዲወጡ አደረገ። ሓውዜን የደረሰው የቦንብ ድብደባ ማንና እንዴት እንደተቀነባበር ብዙ የሚባልለት ቢሆንም የምሬት ጫፍ ሆኖ ህዝብን አሸፍቷል። ዛሬ መጨቆን ያንገፈግፋል ብለው ለትግል በተነሱና በተሰው ታጋዮች ደምና አጥንት ላይ የቆሙ ሌሎች ሓውዜኖች እንዲፈጠሩ አድርገዋል። እያደረጉም ነው።
ይህ በማን ስም እየሆነ ነው? በህወሃት አማካይነት በትግራይ ህዝብ ስም!!
ኦሮሚያ ልጆቿን በእስርና በጥይት እያጣች ነው። በጨለማ ቤት እየተሰቃዩ ያሉ የኦሮሞ ልጆች ግፍ ሰፍሮ ሞልቷል። አማራው አገር አልባ ሆኖ በየጎዳናው እየወደቀ ነው። እየተለዩ ከየክልሉ እየተባረሩ ነው። የመኖር ዋስትናቸውን ተከልክለው በሞትና በጣር መካከል ያሉ ህጻናትና ነፍሰጡሮች ለቅሶ ሰማይ ደርሷል። ይህ ሁሉ አልበቃ ብሎ እስር ቤት የሚማቅቁና የሚሰቃዩ ሰውነታቸውም የሚተለተል አሉ። የተገደሉ አሉ። ይህንን የሚያደርገው ደህንነቱ የተቆጣጠረውና መሳሪያ ያነገተው ኃይል ነው። ይህ ኃይል ደግሞ ህወሃት ነው። ህወሃት ይህንን ሁሉ ግፍ የሚፈጽመው በትግራይ ህዝብ ስም ነው። እያመረተ ያለው ደግሞ ብዙ ሓውዜኖችን ነው። በደልና የበቀል ስሜት ላንድ ጎሳ ወይም ሕዝብ ብቻ የተሰጠ አይደለምና ሌሎችም ሊነሱ ይችላሉ። መቼና እንዴት? አይታወቅም። በሲዳማ፣ በሶማሌ፣ በአፋር፣ … ብዙ ችግርና ምሬት አለ።
በጋምቤላ ግፍ ነዶውን እየወዘወዘ ነው። በጋምቤላ በዘመናት ወደፊት የማናገኛው የደን ሃብት እየወደመ ነው። በጋምቤላ ሰላማዊ ህዝቦች ከቀያቸው እየተፈናቀሉ መሬታቸውን እየተነጠቁ ለውጪ “ባለሃብቶች” እንዲሁም ለትግራይ ተወላጆች እየተከፋፈለ ነው። በባሌ፣ በቦንጋ፣ በወለጋ፣ ድፍን ኦሮሚያና የደቡብ ክልል ደን እየተጨፈጨፈ ትግራይ በደን እየተሸፈነች ነው ብሎ መጨፈር ለትግራይ ህዝብ ኩራት አይሆነውም። ኢትዮጵያዊ ነው የሚባለው የትግራይ ህዝብ እሱ የሚጠላውና ልጆቹን የገበረለት ግፍ በሌሎች ወገኖቹ ላይ ሲፈጸም ዝም ማለቱ ለምንና ከምን የመነጨ እንደሆነ ለማወቅ የሚፈልጉ አሉና ጥያቄውን እናቀርባለን።
ስለመፈናቀል ስናወራ “የትግራይ ተወላጆች ተፈናቀሉ” ሲባልና “ተፈናቀልን” ብለው ቅሬታና አቤቱታ ሲያቀርቡ አንሰማም። ይልቁኑም የአማራን ለም መሬት ለትግራይ በመከለል በደል የሚፈጽመው ህወሃት የሚባለው በትግራይ ህዝብ ስም የተደራጀና በነጻ አውጪ ስም እስካሁን አገር የሚመራ ቡድን ነው። ይህ ሁሉ ሲደረግ የትግራይ ህዝብ ያውቃል። ቢያንስ ቢያንስ የሰው መሬት ወርረው የተቀመጡት አይክዱትም። ግን ይህ እስከመቼ ይቀጥላል? ፍርሃት አለን። ለምን? ይህ ሁሉ ሌላኛው የሓውዜን ክፍል ነዋ!!
ስለ ግብር ሲነሳ የትግራይ ተወላጆች በግብር ዕዳ፣ በባንክ እዳና እንደ ልብ ነጻ ሆኖ በመንቀሳቀስ ችግር ቅሬታ ሲያሰሙ አይደመጥም። በመላው አገሪቱ በኢንቨስትመንት ተሰማርተው በሰላም እየሰሩ ነው። ሌሎች ግን በብሔር ተለይተው መከራ ይደረስባቸዋል። ህወሃት በማንነታቸውና ባመለካከታቸው እየነጠለ ከጨዋታና ከኑሮ መስመር ያወጣቸዋል። የጭቃ ቤት፣ አርሰው የሚበሉበት ከብት፣ ዶሮና በግ ሃብት ተብሎ ይወረስባቸዋል። ይህ እውነት ለትግራይ ምሁራን የተሰወረ አይደለም። ይህም ሌላው ህወሃት በትግራይ ህዝብ ስም በሌሎች ዜጎች ላይ የሚፈጥረው የምሬት ሓውዜን ነው!!
ኮንትሮባንድና ህገወጥ ንግድ ሲነሳ የመጀመሪያው መስመር ላይ ሆነው አገሪቱን የሚያልቡት የቀድሞ ታጋዮችና የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ነጋዴዎች ናቸው። ጤፍ ወደ ኤርትራ በማጋዝ፣ ባህር ዛፍና ቡና በማሻገር፣ የዱር እንስሳትን ቆዳና ቀንድ በመነገድ የተሰማሩት ይታወቃሉ። ብዙ እጅግ ብዙ ማለት ይቻላል። የምናነሳቸው ማሳያዎች ሁሉ የኢኮኖሚ፣ የማኅበራዊ፣ የፖለቲካ፣ … ሓውዜኖች ናቸውና እዚህ ለጊዜው ላይ  እናቁም!!
ሻዕቢያ ድንገት ወረራ አካሂዶ ድፍን ትግራይን ሲቀጠቅጥ፣ ህጻናትን በቦንብ ሲቆላ፣ አገሬ ብሎ የተነሳን ህዝብ በማያውቀው ወንጀል እየሰፈሩ ማሰቃየት ይቆም ዘንድ የትግራይ ህዝብ በቀጥታ ድምጹንና ተቃውሞውን በአግባቡ ማሳየት የሚገባው ወቅት ላይ እንደሚገኝ ይሰማናል፤ ደግሞም እናምናለን። ዛሬ “ውርሱን እንጠብቃለን” በማለት የሚጮህላቸው አቶ መለስ በወቅቱ ክህደት ሲፈጽሙ የደረሰው ዛሬ እየተነጠሉ የሚመቱትና መድረሻ ያጡ ወገኖች ናቸው። ዛሬም ቀበሮ ጉድጓድ ውስጥ ናቸው። በሰባና ሰማንያ ሚሊዮን ህዝብ ልብ ውስጥ የተፈጠሩት ሓውዜኖች ወደ ቁጣ ሲለወጡ አምስት አምስት ሆኖ መደራጀት፣ በስውር መታጠቅና በየሰፈሩ ያሉትን አስተባባሪዎች ስም ለቅሞ በመያዝ “ሳልቀደም ልቅደም” ብሎ መራወጥ አያዋጣም፤ ጊዜው ስለሚያልፍበት የትም አያደርስም። ሓውዜናዊ ህይወት የሚኖር ሕዝብ ከደረሰበት በላይ የሚያጣው ስለማይኖር እንኳን ስለማጣት ስለመኖርም አያስብም፡፡ በዚህ ከቀጠለ የቀን ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር በየቦታው ራሱ ህወሃት የፈጠራቸው ሓውዜኖች መናደፍ መጀመራቸው አይቀርም።
“ህወሓትን እናስቀድም … ጠላቶቻችንን እናጥፋ” በሚል የማያቋርጥ ጥላቻ መቀጠል ተጨማሪ ሓውዜኖችን ከመፍጠር በስተቀር “ጠላትን” ማጥፋት የማይቻል እንደሆነ ከዚህ በፊት በሕዝብ ላይ ተመሳሳይ እርምጃ የወሰዱ ተሞክሮ ማስረጃ ነው፡፡ በበረሃ “ጠላትን እናጥፋ”፤ ሥልጣን ይዞ “ጠላትን እናጥፋ”፤ አገር እየመሩ “ጠላትን እናጥፋ”፤ ኢኮኖሚውን ተቆጣጥሮ “ጠላትን እናጥፋ” … 40ዓመት ሙሉ በ“ጠላትን እናጥፋ” መርህ የሚጓዘው ህወሃት “ጉድጓድ የሚምስ ራሱ ይወድቅበታል” የተባለው የተቀደሰ አባባል ሲፈጸም እንዳየነው ከ70 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ለማጥፋት የሚመኘው ህወሃት የራሱ መጥፊያ የሆኑ በርካታ ሓውዜኖችን ፈጥሯል፡፡
“የ100 ዓመት የቤት ስራ ሰጥተናቸዋል” በሚል በየድረገጹ የሚለጠፉ ተራ ድንፋታና ትዕቢት የሚፈጠሩትን ሓውዜኖች ከማብዛት ውጪ ትርፍ የላቸውምና ወደ ደጉ መንገድ መመለስና ሰብዓዊነትን በማስቀደም፤ ተደጋግፎ መኖርን ማጎልበት ይሻላል ለማለት እንወዳለን። ተሳስበውና ተረዳድተው የሚገነቡት የትም ሆነ የት የአገር ነውና ሁሉም ይኮራበታል፤ ይጠብቀዋል። ተጠቃሚ ይሆንበታል። የሚያምርብንም ይህ ነው። ህወሃት አልሰማም ብሏል። የትግራይ ህዝብ ግን ስማ!! ይህ ሁሉ የሚደረገው በስምህ ነው!!

Mar 20, 2013

አራት አንጋፋ የህወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት በክብር ተሰናበቱ


ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አ.ማ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 11 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) ለቀናት ጉባኤውን ሲያካሂድ የሰነበተው የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ህወሃት በማጠናቀቂያው የፓርቲውን 45 የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ምርጫ እያካሄደ ይገኛል ።
ለዓመታት ፓርቲውን በማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ያገለገሉት አምባሳደር ስዩም መስፍን ፣ አምባሳደር ብርሃነ ገብረክርስቶስ ፣ አቶ አርከበ ዕቁባይና አቶ ዘርዓይ አስገዶም ባቀረቡት ጥያቄና ፓርቲው እየተገበረ ባለው የመተካካት ሂደት መሰረት በአዲስ አባላት እንዲተኩ የወሰነ ሲሆን አንጋፋ አባላቱ በክብር ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ተሰናብተዋል።
ላመንበት ዓላማ በመታገላችንና በመስራታችን አሁን ደግሞ በክብር በመሰናበታበታችን ክብር ይሰማናል ብለዋል አንጋፋ አባላቱ ።
የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ምርጫው ተካሂዶ የድምፅ ቆጠራ እየተከናወነ ይገኛል ።


Mar 19, 2013

የህወሃት/ኢህአዴግ የስለላ መረብ እየተበረበረ ነው ሰነዱን ምዕራባውያን፣ የስለላና የመብት ተቋማት ተርጉመውታል

የህወሃት/ኢህአዴግ የስለላ መረብ እየተበረበረ ነው
ሰነዱን ምዕራባውያን፣ የስለላና የመብት ተቋማት ተርጉመውታል
http://www.goolgule.com/tplf-eprdf-insa-is-under-watch/

“አዲሱ ቴሌ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ/ኢንሳ” በሚል ርዕስ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ያዘጋጀው ጥናታዊ ሪፖርት የታላላቅ አገር የስለላ ተቋማት፣ ለጉዳዩ አግባብ ያላቸው መምሪያዎችና የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ትኩረት መሳቡ ታወቀ። ሪፖርቱን አገራቱ በራሳቸው ቋንቋ በመተርጎም የህወሃት/ኢህአዴግን የስለላ መረብ ከተለያየ አቅጣጫ እየመረመሩት ነው።

የጎልጉል ምንጭ የሆኑ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው እንዳስታወቁት አኢጋን የህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም አዲሱ ቴሌን (ኢትዮ ቴሌኮምን) ከዋንኛው የስለላ መ/ቤት ብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት አገልግሎት በእንግሊዝኛው ምህጻረ ቃል NISS (National Intelligence and Security Service) እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ወይም በእንግሊዝኛው (Information Network Security Agency (INSA) – ኢንሳ) ጋር በማጋባት ስለላው በምን ዓይነት መልኩ እንደሚካሄድ በማመልከት ይፋ ያደረገው ባለ 47 ገጽ ሰነድ የተጠቀሱትን ክፍሎች ቀልብ የሳበው ዘገባው በወጣ ማግስት ነበር።

ሪፖርቱ ይፋ መደረጉን ተከትሎ የሪፖርቱ ባለቤት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዘገባውን ወደ እንግሊዝኛ በመቀየር ሰነዱን የሚጠቀሙ አካሎች እውቅና እንዲሰጡት ተጠይቆ እንደነበር ያስታወሱት የመረጃው ምንጭ፣ አኢጋን ተከታታይ ሪፖርቶችን የማዘጋጀት እቅድ እንዳለውና መረጃው በዋናነት ለኢትዮጵያዊ ወገኖች እንዲደርስ ታስቦ የተዘጋጀ በመሆኑ ለጊዜው የትርጉም ስራው ላይ ትኩረት እንደማያደርግ መግለጹን ተናግረዋል። ይሁንና አኢጋን ሪፖርቱን መጠቀም ለሚፈልጉና ተጨማሪ መረጃ ለሚፈልጉ ለመተባበር ዝግጁ መሆኑን በገለጸው መሰረት ሪፖርቱ ወደ ተለያዩ ቋንቋዎች ለመተርጎም በቅቷል።

ጀርመን፣ እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ካናዳ፣ እና ሌሎች የአውሮጳ መንግሥታ ሪፖርቱን ለራሳቸው ለመተርጎም ቅድሚያውን የያዙ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ኤምባሲ ካላቸው አገሮች መካከል ዋና የሚባሉት አስቀድሞ ከሚያደርጉት ጥንቃቄ በበለጠ ከስላለው መረብ ወጥመድ ውስጥ እንዳይወድቁ የማስጠንቀቂያ መመሪያ ከተላለፈላቸው ሰነባብቷል።

የደህንነቱን ስራ ከቴሌ ጋር በማገናኘት የተካኑትን የቻይና የቴሌኮም ኩባንያዎች በማስገባትና የአውሮፓን የቴሌኮም ተቋማትን “ወግዱ” በማለት ህወሃት/ኢህአዴግ እንዲሰናበቱ ማድረጉ ዋና ርዳታ ሰጪ አገሮችን ቅር አሰኝቷል። ከዚህም በላይ ከቴሌኮም ንግዱ ጎን ለጎን አገራቱን ከመረጃና ከአጋርነት ማግለሉ የፈጠረው ቅሬታ ቀን ጠብቆ የህወሃት/ኢህአዴግን አመራር ዋጋ እንደሚያስከፍለው የመረጃው ባለቤት ጨምረው ገልጸዋል።

የዓለም ታላላቅ አገሮችን ቀልብ የሳበውና ከፍተኛ መረጃዎችን የያዘው ሪፖርት በአገር ጉዳይ ላይ ትኩረት ሰጥተው በሚሰሩ የኅትመት፣ የድረገጽ፣ የድምጽና ምስል መገናኛዎች ሰፊ ሽፋን አለማግኘቱ የሪፖርቱን ባለቤት ብቻ ሳይሆን በትርጉሙ ላይ የተሳተፉትን አገራት የመረጃ ሰዎችን ያስገረመ ጉዳይ እንደነበር፣ ይሁንና በቅርቡ ሪፖርቱ ህይወት ዘርቶ በሁሉም ወገን እንደ ሰነድ የሚወሰድ እንደሚሆን የንቅናቄው የህዝብ ግንኙነት ክፍል ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በላከው የኢሜይል መልዕክት ተናግሯል። በመልዕክቱ ስማቸውን መዘርዘር ባያስፈልግም የተለያዩ የስለላ ድርጅቶችና አገሮች ሪፖርቱ በእንግሊዝኛ ተዘጋጅቶ እንዲሰጣቸው ጥያቄ አቅርበው እንደነበር ክፍሉ ገልጾዋል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ወይም በእንግሊዝኛው (Information Network Security Agency (INSA) አኢጋን ያወጣውን ሪፖርት ተከትሎ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት እለት ድረስ መቃወሚያም ሆነ ማስተባበያ አላቀረበም። ኢንሳ በቻይና የቴሌኮም ኩባንያ ዜድቲኢ አማካይነት የዜጎችን እንቅስቃሴ ወደ መረጃ ቋት ውስጥ በማስገባት የሚያካሂደው ስለላ፣ 


በተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችና አመራሮች ላይ እንዲሁም ኤምባሲዎች ላይ የሚያካሂደው ክትትልና በንጹሃን ላይ 

በሚፈጽመው አፈና በቅርቡ ይፋ የሚወጣ ከየአቅጣጫው ተቃውሞ ሊቀርብበት እንደሚችል ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ አመልክተዋል።

ኢህአዴግ በደቡብ ሱዳን የሚያካሂደውን ጣልቃ ገብነትና ጥቅምን የመጋራት “ወረራ” እና የህወሃት ወገን የሆኑ ነጋዴዎች በጁባ ስለሚያካሂዱት ስለላ አኢጋን በዝርዝር አቀርበዋለሁ ያለውን ተጨማሪ መረጃ አስመልክቶ በጥልቀት እየሰራበት መሆኑን ለጎልጉል አስታውቋል። መረጃውን መቼና እንዴት በምን ዓይነት መልኩ ይፋ እንደሚያደርግ ግን ቀን ቀጥሮ አላስታወቀም።

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ከአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ሕዝብ ግንኙነት ባገኘው ፈቃድ መሠረት “አዲሱ ቴሌና ኢንሳ፡ የህወሃት/ኢህአዴግ የስለላ መረብ” በሚል ርዕስ የወጣውን ዘገባ ከዚህ በታች አቅርበነዋል፡፡ አኢጋን በዘገባው ላይ በግልጽ እንዳስቀመጠው ጽሁፉን “ለማስተማሪነት፣ የቅስቀሳ ዘመቻ ለማካሄድ፣ ለጥናትና ምርምር እንደ ምንጭ በመጥቀስ ያለ ምንም ክፍያ መጠቀም ይቻላል፡፡”
“አዲሱ ቴሌ”
እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት
ኤጀንሲ (ኢንሳ)፡
የህወሃት/ኢህአዴግ የስለላ መረብ

ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ከሚያካሂዳቸው በርካታ ተግባራት በተጨማሪ ላለፉት ወራት የህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ያካሄደውንና ሊያካሂድ ያሰበውን የስለላ ተግባር ሲመረምር ቆይቷል፡፡ በተለይም ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም አዲሱ ቴሌን (ኢትዮ ቴሌኮምን) ከዋንኛው የስለላ መ/ቤት ብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት አገልግሎት በእንግሊዝኛው ምህጻረ ቃል NISS (National Intelligence and Security Service) እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ወይም በእንግሊዝኛው (Information Network Security Agency (INSA) – ኢንሳ ጋር በማጋባት ስለላውን በምን ዓይነት መልኩ ለማካሄድ እንዳሰበ የሚያትት ባለ 47 ገጽ ግርድፍ ዘገባ አቅርበናል፡፡

“አዲሱ ቴሌ” እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ (ኢንሳ)፡ የህወሃት/ኢህአዴግ የስለላ መረብ በሚል ርዕስ የቀረበው ይህ መረጃ በኢትዮጵያችን የተካሄደውንና በመካሄድ ላይ ያለውን የአፈና መዋቅር በጥቂቱ የሚያወሳ ነው። ዘገባው የህወሃት/ኢህአዴግ የደኅንነትና የአፈና ተቋማት ከቴሌኮም አገልግሎት ጋር እንዴትና ለምን እንደተቆራኙ፣ የምዕራብ አገራት የቴሌኮም ቴክኖሎጂ የተገፋበትን ምስጢር፣ አዲሱን ቴሌ ከአገር ወዳዶች በማጽዳት የህወሃት/ኢህአዴግን ፖለቲካና ስውር አጀንዳ ማስፈጸም ይችላሉ ተብለው ለታመነባቸው ክፍሎች ወይም የአገዛዙ “ቁሶች” እንዲዛወር የተደረገበትን ምክንያት፣ በፖለቲካ ድርጅቶችንና ኃላፊዎች እንዲሁም መንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች (መያዶች) ላይ የሚካሄደውን ስለላ በመጠኑ ለማሳየት ጥረት ተደርጓል፡፡

በመጨረሻም ይህንን የስለላ መረብ በመጣስ ሕዝባችን ትግሉን በምን ዓይነት መልኩ ማከናወን እንዳለበትና እንዴት የመረጃ ጫካ ውስጥ በመግባት መደበቅ እንደሚቻል የተወሰኑ ሃሳቦችን ለመዳሰስ ተሞክሯል፡፡

በባህርዳር ጊዮን ሆቴል ጉዳይ የተነሳ የአማራ ክልል ባለስልጣናትና ህወሀት ተፋጠዋል


የዛሬ 21 አመት ህወሀት/ ኢህአዴግ አሸንፎ አዲስ አበባን ከመቆጣጠሩ በፊት ለህወሀት በመሰለል ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረጋቸው የሚታወቁት በባህርዳር ከተማ ነዋሪ የሆኑት የአድዋው ተወላጅ እና የአቶ መለስ ዜናዊ የቅርብ ዘመድ አቶ ወልዱ፣ ለህወሀት  ላበረከቱት አስተዋጽኦ ፣ አቶ መለስ ዜናዊ የመንግስት ንብረት የሆነውን ጊዮን ሄቴልን በ5 ሺ ብር ኪራይ እንዲሰሩበት በገጸ በረከት ስጥተዋቸው ነበር።

አቶ ወልዱ በልጃቸው በአቶ ብስራት ወልዱ ዋና አስተዳዳሪነት ሆቴሉን ሲሰሩበት እና ከፍተኛ ግብር ሲያጋብሱበት ከቆዩ በሁዋላ፣ ህዝቡ በባህርዳር ከተማ አንድ ኪዎስክ በ5 ሺ ብር እየተከራየ ጊዮን ሆቴልን የሚያክል በስፋቱና በጥራቱ ተወዳዳሪ የሌለውን ሆቴል እንዴት መንግስት በ5 ሺ ብር ያከራያል በማለት ተቃውሞ ሲያሰማ መቆየቱን ተከትሎ፣ የፌደራል የኪራይ ቤቶች ድርጅት የክልሉ መንግስት ቤቶች ኤጀንሲ ሆቴሉን እንዲረከብ ለአማራ ክልል ቤቶች አስተዳዳር አምና ደብዳቤ ጽፏል።
ሆቴሉን እንዲያስረክቡ ድብዳቤ የደረሳቸው አቶ ወልዱ  በቀጥታ ለአቶ በረከት ፣ ለፌዴሩሽን ምክር ቤት ሰብሳቢው ለአቶ ካሳ ተክለብርሀንና ለቀድሞው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አዲሱ ለገሰ ፣ የብሄር ብሄረሰቦችን በአል ለማክበር አዲስ አበባ በተገኙበት ወቅት፣ አቶ መለስ ዜናዊ መሞታቸውን ተክትሎ ቤቱን እንዲያስረክቡ መጠየቃቸውን በመናገራቸው፣ ባለስልጣኖቹ የክልሉ መንግስት የጻፈውን ደብዳቤ እንዲያነሳ መጠየቃቸው ታውቋል።
የክልሉ ቤቶች ኤጀንሲ ጉዳዩ ከፍተኛ ዝርፊያ መሆኑን ቢገልጽም፣ የሆቴሉ አስተዳዳሪ የአቶ ወልዱ ልጅ ብስራት ወልዱ የክልሉን ባለስልጣናት በማስፈራራት እርምጃ እንደሚወስድ በመዛት ሆቴሉን ለማስረከብ ፈቃደኛ እንደማይሆን በመግለጹ ክልሉ የሚያደርገው ጠፍቶት ተቀምጧል። የከተማው ህዝብ በበኩሉ የክልላችንን ባለስልጣኖች አንድ የህወሀት አባል ሰው እንደልቡ እያሽከረከራቸው  በማለት ትችት እያቀረበ ነው። ህዝቡ በተደጋጋሚ የሆቴሉን ጉዳይ አንድ እልባት እንዲሰጠው እየጠየቀ ቢሆንም፣ የክልሉ ባለስልጣናት ምንም ማድረግ እንደማይችሉ እያስታወቁ ነው።
የጊዎን ሆቴል በጣና ዳር የተሰራ በርካታ አልጋዎችን በቀን ከ175 እስከ 250 ብር በሚደርስ ዋጋ ለቱሪስቶች የሚያከራይ፣ የአገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ወደ ሆቴሉ ሲሄዱ በነጻ የሚስተናገዱበት፣ በውስጡ የያዘው ቡናና ፍራፍሬ ከፍተኛ ገቢ የሚያስገኙ ዘመናዊ ሄቴል ነው። የድርጅቱ የቀን ገቢ በ10 ሺዎች የሚቆጠር ቢሆንም ፣ ባለሀብቱ በወር የሚከፍሉት የኪራይ መጠን 5 ሺ ብር ብቻ ነው። ጭቅጭቅ ከተነሳበት ከአምና ጀምሮ ደግሞ ባለሀብቱ የአምስት ሺ ብር የቤት ኪራይ መክፈል ማቆማቸው ታውቋል።
ከምንም የተነሱት የሆቴሉ ባለቤት ከ21 አመታት በሁዋላ እጅግ የናጠጡ ሀብታም ለመሆንና የተለያዩ ድርጅቶችንም ለመክፈት ችለዋል።
ጉዳዩን በማስመልከት ጥያቄ ያቀረብንለት አንድ የኪራይ ቤቶች ድርጅት ሰራተኛ ” ግለሰቡ ቤቱን እንዲያስረክቡ ሲጻፍላቸው ዋጋህን ታገኛለህ” የሚል መልስ መስጠታቸውን ገልጿል። የክልሉ መንግስት እየደረሰበት ካለው ትችት ነጻ መሆን የሚችለው ግለሰቡ ሆቴሉን እንዲያስረክቡ ሲያደርግ እና እንደማንኛውም ሰው ተጫርተው ተገቢውን ክፍያ መክፈል ሲችሉ ብቻ ነው” ብሎአል።
አንድ ሌላ የባህርዳር ነዋሪ ደግሞ  ጊዮን ሄቴል ህወሀት በክልላችን ያለውን የበላይነት ለማሳየት ጥሩ ምሳሌ ነው ብሎአል።
በጉዳዩ ዙሪያ የሆቴሉን ባለቤትም ሆነ የክልሉን መንግስት ለማግኘት ያደርገው መኩራ አልተሳካም። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚታየው የአንድ ዘር የኢኮኖሚ፣ ወታደራዊና ፖለቲካዊ የበላይነት የአገሪቱ መነጋጋሪያ እየሆነ መምጣቱን መዘገባችን ይታወሳል።
source: ኢሳት ዜና: 

The following is from his blog

The Boss of Bahir Dar: Bisrat at the Ghion Hotel

If you need to get anything arranged in Bahir Dar, go and see Bisrat at the Ghion Hotel. He is a fabulous man who manages the Ghion Hotel (a budget hotel with a beautiful lakeside patio and a wonderful, relaxed vibe). Even though we did not stay at the Ghion (it is an older hotel in need of some renos), Bisrat arranged our tour to the Blue Nile falls and organized our trip back to Addis (the Ghion tours to the Blue Nile Falls are listed in the Lonely Planet). Our discovery of Ato Bisrat was a wonderful side-benefit of visiting the Ghion.

When we called and complained about our shady mini-bus driver (Iago), Bisrat took immediate action and said he would handle the situation, promising even to return our deposit. Bisrat is one of those people you meet in life that goes out of his way to help you even if he does not have to. He did not gain by helping us (in fact he might still have to endure the drama associated with Iago), but he helped us just the same. If you visit Bahir Dar and you should (it is stunning), call Bisrat. He will help you out. Who’s the Boss in Bahir Dar? No, not Tony Danza or Judith Light. It’s Bisrat.

from American observer 

   I keep thinking I should be coming up with deep thoughts and Truths about what being in Africa is about, but I’ve only been here a week or so and am still feeling my way. But what about this: at the Ghion Hotel I proofread and edited some documents for Bisrat, the manager in exchange for a hot shower in his office and a discount on a boat trip the next morning—and I don’t even stay at the Ghion!
     The point is to have the liberating feeling that anything is possible. Tomorrow I may feel the opposite, but just to have the feeling, however fleeting it may prove to be, makes being here exciting.     
                                                                                                   Doesn't Bisrat look like Charles Barkley?


     Everyone gravitates to the Ghion. It has an ideal, relaxed setting next to Lake Tana, good food, cold drinks, soothing breezes and horrendous mosquitoes at dusk. Bisrat is a fixer, able to arrange everything you could need: transport, hotels, tours, communications, etc. I like him because he not only looks like Charles Barkley, especially when he raises his eyebrows, but he has a sense of humor that I like.
     He had an employment poster for a new hotel opening in Addis Ababa and I said he shouldn’t show it to his staff or they might leave. Without missing a beat, he deadpanned, “I hope they leave.”
     He made a call for me to a hotel in the next town I am going. While on the line he said to me, “They’re full.” As a joke I said, “Tell them I’m American.”
     In an authoritarian voice he barked into the phone, “He’s American!” and then with professional comic timing, “Hello?” faking that they hung up on him.
  

ጄኔራል ግራዚያኒን ኃውልት ግንባታ ተቃዉመዉ ከታሰሩት ሰልፈኞች አንደበት

ቀይ ለባሾቹ ሰልፈኞች የታጎሩት በአራዳ ፖሊስ መምሪያ ጊቢ ውስጥ ነበር

(በበፍቃዱ ኃይሉ)
EMF – መጋቢት 8/2005 የባለራዕይ ወጣቶች ማኅበር እና የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የኢትዮጵያውያን ጠላት የነበረው የፋሺስት ጣሊያን ጄኔራል ግራዚያኒን ኃውልት (በጣሊያን አገር፣ የትውልድ መንደሩ አካባቢ) መቆም በመቃወም የሰልፍ ጉዞ ከስድስት ኪሎ (የካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ ኀውልት) እስከ ጣሊያን ኤምባሲ ድረስ ለማድረግ እየተንቀሳቀሱ ነበር፡፡ የሰልፉ ተሳታፊዎች ከጀርባው ላይ ‹‹ለግራዚያኒ ኀውልት ማሠራት አባቶቻችን የከፈሉትን መስዋዕትነት ማራከስ ነው›› የሚል ጽሑፍ የታተመበት ቀይ ቲ-ሸርት ለብሰው ነበር፡፡ የኢሕአዴግ ካድሬዎች ደግሞ ‹‹ይቺ ባቄላ…›› በሚል ምክንያት ነው መሰለኝ ‹‹የተቃውሞ ሰልፍ…›› የሚባለውን ነገር ለማስቆም ራሱ ግብግብ ፈጠረ፣ ወጣቷ ዓለምን የቀን አጋጣሚ ስድስት ኪሎ አካባቢ፣ በዕለተ እሁድ (መጋቢት 8/2005) አንቀዥቅዦ አመጣት፡፡ የለበሰችው የአዘቦት ቀይ ቲ-ሸርት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ለመዋል ምክንያት ይሆነኛል ብላ አልተገመተችም ነበር፡፡ ፌዴራል ፖሊስ ቀይ ለባሾቹን ማፈስ ሲጀምር ዓለምንም አብሮ አፍሶ አጋዛት፡፡
ቀይ ለባሾቹ ሰልፈኞች የታጎሩት በአራዳ ፖሊስ መምሪያ ጊቢ ውስጥ ነበር

በተመሳሳይ ሰዓት ለሥራ ጉዳይ ጓዙን ጠቅልሎ ወደአፋር ለመጓዝ እየጠበቁት ያሉ ባልደረቦቹን ለማግኘት በታክሲ ውስጥ ይጓዝ የነበረ አንድ ሰው ከስድስት ኪሎ ተነስቶ አምስት ኪሎ እስኪደርስ የተመለከተውን ሁካታ ዓይቶ ላለማለፍ ከታክሲ ይወርዳል፡፡ ፖሊሶች ከሰልፈኞቹ ውስጥ አሳደው የያዙትን እያፈሱ መኪና ውስጥ ሲያጉሩ፣ ከፖሊሶች ዕይታ እየተሰወረ በሞባይሉ ፎቶ ለማንሳት ሲሞክር፣ አንድም የረባ ፎቶ ሳያነሳ በሦስተኛው ፎቶ ላይ ከፖሊሶች ጋር ዓይን ለዓይን ተጋጠመ፡፡ እሱም ተይዞ ተከተላቸው፡፡ ይህ ድንገተኛ እስረኛ የዚህ ጽሑፍ ጸሐፊ ሆነ፡፡
የታፈሱት ሰልፈኞች ሁሉ የታጎሩት በአራዳ ፖሊስ መምሪያ ጊቢ ውስጥ ነበር፡፡ ጊቢው ውስጥ እንደደረስኩ ከፊት ለፊቴ ደረጃው ላይ የተኮለኮሉትን ሰልፈኞች ተመለከትኩ፡፡ ወጣቶቹ ታፍሰው የገቡ ሳይሆን ወደው የተሰበሰቡ ይመስሉ ነበር፡፡ እንዲያውም በገባሁ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ጮክ ብለው ይዘፍኑ ጀመር፡-
‹‹… ተከብረሽ የኖርሽው ባባቶቻችን ደም፣ ባባቶቻችን ደም
እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም…››
በዚህ ጊዜ ከፖሊሶቹ አንዱ አብሮ ሲዘምር ይታይ ነበር፡፡ ፖሊሶቹ የተሻለ ትሁቶች ቢሆኑም፣ ሲቪል ለባሾቹ ግን ማመናጨቅ እና ማዋከብ ዋነኛ ሥራቸው ነበር፡፡ እኔን በመኪና ይዘውኝ ከመጡት ውስጥ አንዱ ‹‹ዴሞክራሲ በዛ…›› የሚለውን ቃል እየደጋገመ በቁጭት ይናገራል፡፡ ብዙዎቹ የመምሪያው ፖሊሶች ከየት እንደመጣ የማያውቁት ኮማንደር ግን የተቆጨው በመዘግየቱ ነው፤ ‹‹ይሄን ያክል እስኪሰባሰቡ መቆየት አልነበረብንም›› አለ – እኔው ጎን ቁጭ ብለው ሲነጋገሩ፡፡ በሬዲዮናቸው ሲለዋወጡ ከነበረው ውስጥም ‹‹ሱማሌ ተራ የተጎዳውን ሰውዬ የት ወሰዳችሁት?… ተክለሃይማኖት ሆስፒታል?…›› ይባባሉ ነበር፡፡ በዚሁ ጉዳይ ይሁን አይሁን ግን ‹‹መረጃም (ማስረጃም)›› አልነበረኝም፡፡
ጊቢው ውስጥ ከሌሎቹ እንዳልቀላቀልና ብቻዬን እንድቆይ አድርገውኛል፡፡ ባንድ በኩል ስልኬ ላይ ያሉትን ፎቶዎች አጥፍተው ይፈቱኛል፣ ጉዞዬም ይቀጥላል በሚል ደስ ብሎኛል፡፡ በሌላ በኩል በዓይን የማውቃቸውን እነዚያን ልጆች ቀረብ ብዬ አለማነጋገሬ ቆጭቶኛል፡፡ በዚህ መሐል ግን ሁሉም እየሄዱ ቃል ሲሰጡ ቆዩ (ቃል ሲባል ቃል እንዳይመስላችሁ፤ ከስም አንስቶ የኔ የምትሉትን ነገር በሙሉ ይጠይቋችኋል)፤ ከዚያም የኔም ተራ ደረሰና ቃል ሰጥቼ ሳበቃ እኔም በቀላሉ እንደማልሰናበት ሲያረዱኝ የጓዝ ኮተቴን ሁሉ አስመዝግቤ እዚያው ተጠቃለልኩ፡፡
ከዚያም ቃል የመስጠቱ ሥነ ስርዓት ቀጠለ፤ የመጣው ሁሉ በራሱ መንገድ ያንኑ ጥያቄ መልሶ፣ መላልሶ እያንዳንዱን ታሳሪ (ተጠርጣሪ ልበል ይሆን?) ይጠይቃል፤ እያንዳንዱም ተጠርጣሪ ይመልሳል፡፡ ሆኖም ብዙዎቹን መርማሪዎች የብስጭት መንስኤ የሚሆን ነገር ባለራዕዮቹ ወጣቶች ሳይናገሩ አይወጡም ነበር፡፡ ብሔር ሲባሉ ‹‹ኢትዮጵያዊ›› ይላሉ፡፡ ይህንን የሚሉት ‹‹ብሔር›› የሚለው ቃል ከግዕዝ የተወሰደ ሲሆን፣ ትርጉሙም ‹‹አገር›› መሆኑን እያጣቀሱ ነው፡፡ ታዲያ ይህ አባባል ለመርማሪዎቹ የሚያበሳጭ ድፍረት ነበር፡፡
ፖሊሶቹ የሆነችውን ሁሉ እየደወሉ፣ ለአለቆቻቸው ይናገራሉ፡፡ ከዚህ መሐል ከሰልፈኞቹ አንዱ ለብሶት የነበረው ባንዲራ ላይ በእስክርቢቶ የጻፈውን ደብዳቤ ከስልኩ ወዲያ ላለ ሰው በንባብ ሲያጽፉት ሰምቻለሁ፡፡ ጽሑፉ ባብዛኛው መንፈሳዊ ነው ቢባል ይቀላል፡፡ ‹‹ለእመቤታችን በአስራትነት የተሰጠችው አገራችን ኢትዮጵያ…›› ብሎ ነው የሚጀምረው፡፡
ምርመራው/ጥያቄው ቀጥሏል፤ ከጠያቂዎቹ መካከል የደኅንነት እና የኢንሳ ሰዎችም ነበሩበት፡፡ ከጥያቄዎቻቸውም ውስጥ የኢሜይል አድራሻ እና የይለፍ ቃል፣ የፌስቡክ አድራሻ እና የይለፍ ቃልም ይጠይቁ ነበር፡፡ እያንዳንዱ ታሳሪ (ተጠርጣሪ አልልም) ስሙን በቪድዮ ካሜራ ፊት እንዲናገር ይገደድ ነበር፡፡ እንግዲህ ይህንኛው መጀመሪያ ላይ እያንዳንዱ ሰው ከተነሳው ፎቶ በተጨማሪ መሆኑ ነው፡፡ በዚህ የጅምላ እስር ውስጥ ካስተዋልኳቸው ጉዳዮች ውስጥ የሴቶቻችንን ጀግንነት ነበር፡፡ ለምሳሌ፣ እኔ ያለምንም ማንገራገር ምስሌን አስቀርጬ ወደቃለመጠይቁ ሳልፍ የሰማያዊ ፓርቲዋ አመራር አባል ሐና ዋለልኝ ‹‹አልቀረጽም፣ አሻፈረኝ›› ብላ ስትሟገት ድምፅዋ ይሰማኝ ነበር፡፡
ሲመሽ ይፈቱን ይሆን? እዚሁ ያሳድሩን ይሆን? ሌላ ቦታ ይወስዱን ይሆን? ምን ብለው ይከሱን ይሆን? እየተባባልን የተሰባሰብንባት አንዲት በረንዳ መሳይ ክፍል ውስጥ፣ ኢቴቪ በቀጥታ የሚያስተላልፋቸውን የአዳማ እና የመቐለ የኦሕዴድ እና የሕወሓት ስብሰባዎች መኮምኮም ጀመርን፡፡ አሳሪዎቻችንም በስልክ አለቆቻቸውን እያነጋገሩ ሽር ጉዳቸውን አጧጡፈውታል፡፡ ኢቴቪም ብቻውን በዓሉን ማክበር አልቻለም፡፡ መብራቱ ብልጭ ድርግም አበዛ፡፡ ብልጭ ድርግም አልኩ እንጂ ያበዛውስ ድርግም ማለት ነው፤ አልፎ፣ አልፎ ግን ላፍታ ብልጭ እያለ ነበር፡፡ በጨለማው ውስጥ ራታችንን በጨለማ ተቋደስን፡፡ ሁላችንም ምሳ ያልበላን ቢሆንም አንዳንዶች ግን ቁርሳቸውንም አልበሉም፡፡
የመታሰራችን ዜና በማኅበራዊ አውታሮች በመጠኑ ቢስተገባም የብዙዎቻችን ቤተሰቦች ግን አልሰሙም፤ ደውሎ የማሳወቅ ዕድሉም አልተሰጠንም፡፡ እዚያው ጨለማ ውስጥ ከቆየን በኋላ ወደ 3፡00 ሰዓት ገደማ ወደ ጃንሜዳ አካባቢ የሚገኝ ማረሚያ (እስር ቤት) በሁለት ዙር ተወሰድን ከ30 በላይ እስረኞች አንድ ላስቲክ ብቻ ወለሉ ላይ የተነጠፈበት ክፍል ውስጥ ብንታጎርም በእርስ በርሳችን ጫወታ ተጠምደን ነበር፡፡ (በነገራችን ላይ እኛ ወደዚህ እስር ቤት ስንዛወር ቀይ ለባሽዋ ዓለም ተለቅቃ ወደቤቷ ሄዳለች፡፡) የሄድንበት በሰልፉ ዋዜማ ሲቀሰቅሱ ከታሰሩ ሌሎች ጋር ተቀላቅለናል፡፡ የጅምላ እስሩ ጉዳይ በዋዜማው እንደተጀመረ ያወቅኩትም ያኔ ነው፡፡ ቀድመው ከታሰሩት ውስጥ ሁለቱ ክፉኛ ቡጢ እና ካልቾ ቀምሰው እንደሆነ ለማወቅ እስኪናገሩ መጠበቅ አያስፈልገንም ነበር፤ የአንደኛው ጃኬት የደረቀ ደም ከፊትለፊት ይታይበታል፡፡
ለአምስት ሰዓት ዐሥራ አምስት ደቂቃዎች ሲቀሩት ግን እንደገና እንድንንቀሳቀስ ተነገረን፡፡ ከኛ ቀደም ብለው ሴቶቹም ወደቀጨኔ (ችሎት መድኃኔዓለም ኮንዴሚኒዬም አጠገበ ያለ) ወረዳ 9 ማረሚያ ቤት እንደተወሰዱ እና ከኛም ውስጥ 12ቶቻችን መከተል እንዳለብን ተነገረን፡፡ እዚያ እንደደረስን ግን ምነው እዚያው በቀረን የሚያስብል ትዕይንት ገጠመን፡፡ እያንዳንዱ ክፍል እላይ በላይ ተደራርበው በተኙ እስረኞች ተጨናንቋል፡፡ ሌላው ቀርቶ ጫማ ማስቀመጫ ቦታ እንኳን በክፍሉ ውስጥ ስለሌለ ጫማዎቻችንን ውጪ እያስቀመጥን እንድንገባ ተገደድን፡፡ ሦስቱ (አራት ሜትር በአራት ሜትር የሚገመቱ) ክፍሎች ውስጥ አንዱ 37፣ አንዱ 34 እና ሌላኛው ውስጥ 30 እስረኞችን ይዟል፡፡
እንዳጋጣሚ 30 ሰዎች የያዘው ውስጥ ነበር እኔ የደረሰኝ፡፡ የኛ ክፍል ይሻላል ተብሎ ዶ/ር ያዕቆብንም አመጧቸው፡፡ ጉዳዩ በጣም አሳዛኝ ነበር፡፡ እኛስ ባልደከመ ጉልበታችን እንችለዋለን፤ ለርሳቸው ግን በጣም ፈታኝ እንደሚሆን መገመት ቀላል ነው፡፡ ክፍሉ በጣም ጥቅጥቅ ብሎ ከመሞላቱ የተነሳ ለኛ ቦታ ለማግኘት የቤቱ ካቦ ተነስቶ እያንዳንዱን እስረኛ እየቀሰቀሰ ማጠጋጋት ነበረበት፡፡ በቦታ ጥበት ምክንያት ደረቁ ወለል ላይ በአንድ ጎናችን እንድንተኛ ከመገደዳችን የተነሳ እኔ ይህን ጽሑፍ እስከምጽፍበት ሰዓት ድረስ ቁርቋሬው የፈጠረው ሕመም ጎኔን አያስነካኝም፡፡ ካቦው አጠጋግቶልን ሲጨርስ ሁላችንንም የገቢ ገንዘብ ተቀበለን እና ተኛን፡፡ እዚያ ክፍል ውስጥ መተኛት ማለት፣ መተኛት ማለት አይደለም፡፡ የክፍሉ መታፈን እና አስቀያሚ ጠረን፣ ሙቀት፣ በዚያ ላይ እየተቀባበሉ የሚያጨሱት ሲጃራ ጢስ፣ ከዚያ እና ከዚህ የሚተኮስ የፈስ ሽታ… ብቻ የአበሳ ናሙና ነበር፡፡ ሌሊቱን ሲዘንብ ማደሩ ግን በከፊልም ቢሆን የክፍሉን አየር አቀዝቅዞታል፤ ችግሩ ዝናቡ ውጪ ያስቀመጥነው ጫማ ውስጥ ውኃ መሙላቱ ብቻ ነበር፡፡
እንደምንም ነጋልንና ወደፍርድ ቤት እንደምንሄድ ተነግሮን ጥንድ ጥንድ እየተደረግ በካቴና ተቆላለፍን፡፡ ከመሐከላችን አንዱ የማኅበሩ አባል፣ ፀጉሩን አጎፍሮ ስለነበር (ለፍርድ ቤቱ ውበት አይመጥንም ብለው ይሆናል) ይቆረጥ አሉና መቀስ አንስተው ይከመክሙት ጀመር፡፡ ፀጉሩን ቆርጠው ሲጨርሱ አሰለፉንና ካቴናችንን ፈቱት፡፡ ‹‹ፍርድ ቤት መወሰዳችሁ ቀርቷል፣ ምናልባት ፖሊስ ጉዳዩን ይፈታዋል›› ተባልንና ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ወደጃንሜዳ ማረሚያ ቤት መልሰው ወሰዱን፡፡ እዚያ ስንደርስ ለፖሊስ ዋስ እያቀረብን እንድንፈታ ተፈቀደልን፡፡ ቀድሞውንም የታሰርነው ያለወንጀል በመሆኑ አስገራሚ ውለታ አልነበረም፡፡
የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ የሚያስፈልገው ቅድመ ሁኔታ ለመስተዳድሩ ማሳወቅ ሲሆን፣ መስተዳድሩ ደግሞ በ24 ሰዓት ውስጥ ‹‹አይሆንም›› የሚል ደብዳቤ ካልጻፈ እንደተፈቀደ ይቆጠራል፡፡ ስለዚህ ሰልፍ ማድረጉ ሕጋዊ ስህተት የለበትም፣ ጉዳዩ ባንድ ጀምበር የተወለደ ሳይሆን ጋዜጦች ዜና የሰሩለት፣ ቁጥቦቹ ሬድዮዎች ሳይቀሩ ያወሩለት ጉዳይ ስለሆነ ወንጀል ነው ፍርድ ቤት ሊያቀርቡት አይችሉም/አይገባቸውምም፡፡ ነገር ግን ‹‹…ካፈርኩ አይመልሰኝ…›› ይመስላል በዋስትና እንድንፈታ ፈቅደው ያገቱብንን ንብረቶቻችንን እየመለሱ መጋቢት 9/2005 እኩለ ቀን ላይ አሰናበቱን፡፡

Mar 18, 2013

“ለምንድነው የኢትዮዽያ የፖለቲካ ድርጅቶች እንደኣሸን የሚፈሉ?”


‎! …….. የኢትዮዽያ ፖለቲከኞች ………!
ጥያቄ , “ለምንድነው የኢትዮዽያ የፖለቲካ ድርጅቶች እንደኣሸን የሚፈሉ?”
በኢትዮዽያ የፖለቲካ ድርጅቶች (ፓርቲዎች) ኣመሰራረት ርእዮተ ዓለም (Ideology) ወይ ሳይንሳዊ መርህ መሰረት (Principle based) ያደረገ ሳይሆን በዘረኝነት ወይ ጎሰኝነትና ጎጠኝነት የተቃኘ በመሆኑ ነው። የዚ ሁሉ ምክንያት ምንድነው?
1) የማህበረሰቡ የፖለቲካ ንቃተ ህሊና ማነስ ነው። በኢትዮዽያ መርህ መሰረት ያደረገ ፖለቲካ ማራመድ የህዝብ ድጋፍ ኣያስገኝም። የፖለቲካ rationality የለም። ድጋፍ ለማግኘት የጎሰኝነትና ጎጠኝነት ቅስቀሳዎች ጠቃሚ ናቸው። ‘እንደዚህ ተበደልን፣ እንዲህ ኣረጉን …’ ስትል የህዝቡን ስሜት (ወይ ቀልብ) መግዛት ትችላለህ። የተለያየ ጎሳና ጎጥ የተለያየ ፓርቲ ያመርታል። ለምሳሌ ህወሓት ድጋፍ የሚሰበስበውና ስልጣን የያዘው በዚ መንገድ ነው።
2) የኣብዛኞቹ ፖለቲከኞች ዋና ዓላማ ስልጣን መሆኑ ነው (ስልጣን መያዝና መሪ ሁኖ መከበር በቃ)። ለዚህም ጥሩ ኣማራጭ የየራሳቸው ፓርቲ በመመስረት የፓርቲው ሊቀመንበር (ፕረዚደንት) መሆን ያምራቸዋል። ለዚህም ነው በሀገራችን እነዚህ “33 የተቃዋሚ ፓርቲዎች “ የሚባሉ ጨምሮ ከ60 በላይ ፓርቲዎች ኣሉ የሚባለው።
3) የገዢው ፓርቲ ሴራዎች:: ህወሓት/ኢህኣዴግ ጥሩ ነገር በመስራት ተቃዋሚዎችን ለማሸነፍ ከመሞከር ይልቅ የመንግስትን ሃብትና መዋቅር በመጠቀም ተቃናቃኞችን በማፍረስና ማዳከም ሴራ መጠመዱ ሌላው ምክንያት ነው። በሚያደርገው በስለላ የተደገፈ conspiracy የተቃዋሚ መሪዎች (የገዢው ፓርቲ የጥፋት ስራ መሆኑ ስለማይገነዘቡ) እርስበርሳቸው እንዳይተማመኑና ኣንድነት እንዳይፈጥሩ ስለሚያደርግ ነው።
4) የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሳሳተ የትግል ኣቅጣጫ (Game Theory)። ኣንዳንድ ፖለቲከኞች (እንዳውም ኣብዛኞቹ) የህዝብን ስሜት ለመግዛት ሲባል ዘረኝነትን የሚቃወሙ እየመሰሉ በተግባር ግን ራሳቸው ዘረኝነትን (ጎሰኝነትን) ያጠቃቸዋል። እንደውጤትም ሁሉም ዘረኛ ሁነው ይገኛሉ። ሌሎች ከነሱ ጋ ከመቀላቀል ይልቅ ከነሱ ራሳቸው ለመከላከል ሲሉ ሌላ ድርጅት መመስረት ይፈልጋሉ። ፓርቲዎችም ይበዛሉ።
ለምሳሌ
(ሀ) ኣንዳንድ ዘረኝነት ወይ ጎሰኝነትን እንቃወማለን፣ በዘር መከፋፈል ይቅር እያሉ የሚሰብኩ ኋይሎች ግንቦት -7 ከዴምህት (ዴሞክራሲያዊ ምንቅስቃስ ህዝቢ ትግራይ ወይ የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ) ኣብሮ እየተንቀሳቀሰ ነው ብለው ይከሳሉ (ይወቅሳሉ)። ይሄ ፓርቲዎች በዘር ተከፋፍለው እንዲቀሩ ያደርጋል።
(ለ) ህወሓት/ኢህኣዴግ በራሱ ጎጠኝነትን እቃወማለሁ እያለ “ዓረና ትግራይ ፓርቲ ከጠላቶቻችን ሸዋ ፖለቲከኞች በማበር የትግራይን ህዝብ ለመግደል እየተንቀሳቀሰ ነው “ በሚል ስም ያጠፋል። ታድያ ዓረና ፓርቲ ኮ ትግራይ የመገንጠል ዓላማ የለውም፤ ከሌሎች የኢትዮዽያ እህት ፓርቲዎች ይሰራል እንጂ ለብቻው መሆንኮ ኣይደገፍም። ኣብሮነት ጥሩ ነው። ዙሮዙሮ ግን ይሄም ፓርቲዎች እንዳያብሩ ምክንያት ይፈጥራል።
(ሐ) ሰመያዊ ፓርቲ የመሰረቱ ፖለቲከኞች (እንደሚባለው) የኢትዮዽያ ኣንድነት ይሰብካሉ። ዘር ወይ ጎሳ መሰረት ያደረገ ፓርቲ እንደማይደግፉም ይነገራል። እነዚህ ሰዎች ታድያ (የሰማሁት ትክክል ከሆነ ምክንያቱም እንደዚህ ዓይነት ኣስተሳሰብ ከፖለቲከኛ ኣይጠበቅም) የኣንድነት ፓርቲ ኣባላት የነበሩ ሲሆን ፓርቲው (ኣንድነት) እነሱ የማይፈልጉዋቸውን ሰዎች (እነ ስየ ኣብርሃ የትግራይ ተወላጆችን በኣባልነት ስለያዘ) ከፓርቲው ለቀው በመውጣት “ኣዲሱ”ን ሰማያዊ ፓርቲ መሰረቱ። (የፓርቲዎች ቁጥር ጨመረ)።
ይህንን መረጃ (ምሳሌ ‘ሐ’) ትክክል ከሆነ ማለትም ሰመያዊ ፓርቲ ከሌሎች ብሄሮች (ለምሳሌ ትግራይ) በኣባልነት ካልተቀበለ መጨረሻው ምን ሊሆን ነው? እንበልና ሰማያዊ ፓርቲ ስልጣን ያዘ (የኣንድ ፓርቲ ዓላማ ስልጣን መያዝ ስለሆነ) ከዛ እንዴት ኣድርጎ ሀገርን ያስተዳድራል? ወይስ ኣማራ ክልልና ኣዲስ ኣባባ ብቻ ገንጥሎ ሀገር ሊመሰርት ነው?
ጎሰኝነት ወይ ዘረኝነት ኣንቀበልም ስንል ከተለያዩ ብሄሮች በኣባልነት ኣንቀበልም ማለት ሊሆን ኣይገባውም። በኣጭሩ በኢትዮዽያ ፓርቲዎች እንደ ኣሸን የሚፈሉ ገዢ የሆነ ርእዮተ ዓለም መሰረት ያደረገ የፓርቲ ስርዓት ስለሌለ ነው።
በመጨረሻም
በኢትዮዽያ ፓርቲዎች የሚመሰረቱ በርእዮተ ዓለም ልዩነት ምክንያት ኣይደለም ካልን ታድያ የጋራ ነጥባቸው ምንድነው? በኢህኣዴግ ሙስና መሰረት ያደረጉ ጥቅማጥቅሞች ያገናኛቸዋል። የተቃዋሚ ፓርቲዎች ኣንድ የሚያደርጋቸው ነጥብ ደግሞ ገ ዢውን ፓርቲ መጥላታቸው ነው።
የመጨረሻ መጨረሻ
በመርህ የሚንቀሳቀሱ ፖለቲከኞች የሉም ማለት ግን ኣይደለም። ይኖራሉ ግን የህዝብ ተቀባይነት በቀላሉ ለማግኘት ይቸገራሉ። ስለዚ ኣናያቸውም።
የኢትዮዽያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሆይ፡ እባካቹ ኣንድ ጠንካራ ድርጅት ፍጠሩ። 33፣65 እየተባላቹ ኣታሳፍሩን።
It is so!!!     Abraha Desta from Mekele 

TPLF’s Hidden Support to Al-Shabab Exposed


By Orion Asmelash
Truth by nature is self-sustained, it does not get old as time goes, nor does it get defeated by the majority, as evil and deceptions get stronger, truth shines more splendidly in the middle of a great confusion and lies. With all that propaganda regarding Al-shabab since 2006, who would imagine what was hidden underneathTPLF’s closets concerning the mysterious dirty affairs it has with Al-shabab?, and who would think that TPLF would work both with Al-shabab and the so called TFGand other ethnic Somalia groups to keep the fire burning?, Well, It is only through time and crisis that truth became more clearer. The international community has been misled big time when it comes to Ethiopia’s doctrine on Somalia. Ethiopia’s Claim of fight against Al-shabab and terrorism is a big lie and deception. Ethiopia neither want Al-shabab to take over Somalia and nor does it want Al-shabab to desist or die. TPLF cannot survive without terrorism. It is through this that the regime got support from the west and stayed in power for 20 years. The people in the horn of Africa knows TPLF from head to foot, they are familiar with its tactics and games. Anyone who observed TPLF’s behavior for the last 20 years will hardly miss what is behind the scene. TPLF leaders and their followers are like a chameleon, they change colors every season but their aim and real character is always the same. Their mind produces nothing good than fertilizing evil thoughts of bigotry and dirty plots. What TPLF says and does is always the contrary. When they say it is good, it means evil; when they tell you it is dark, it means light; when they say it is bitter, it is sweet. When they call for peace, it means for war; when they advocate for justice, it means they have made crimes; when they denounce terrorism, it means they want it. It is always the opposite. They have a very long and extrudable tongue to deceive and mislead others, but for those who know them very well, deep inside their thoughts “they hatch the eggs of vipers and spin a spider’s web”.
TPLF’s music of “Al-shabab” has become like a national anthem. Is TPLF fighting Al-Shabab or supportingETHIOPIA: TPLF’s Hidden Support to Al-Shabab Exposed it? Well, for those who know TPLF’s character it is not hard to scramble their words and speeches. The people in the region have seen the egg long ago before it got hutched. Today, even little children know how to solve TPLF’s cross words. Unless the international community and specially United States are intentionally cooperating or bypassing TPLF’s hidden agenda, it is not difficult to understand the regime’s strategy in Somalia and the region in general. Considering TPLF’s behavior and past track records, including its terrorism activities, such as abducting aid workers, kidnapping foreigners and robbing up banks while they were rebel fighters against the Mengistu Regime before 1991, it is therefore logical to suspect and enquire to see if there is any reason why TPLF would like the spirit of terrorism to continue exist and live in the region. This is not speculation or conspiracy theory; I am not the first to claim this either. I will let the facts speak for themselves. In 2008, South African Ambassador to the United Nations, Dumisani Kumalo, who was basically the chairman of the U.N. Security Council’s Somalia sanctions committee at that time, in his remarks to the Security Council’s said:
“Eighty percent of ammunition available at the Somali arms markets was supplied by TFG and Ethiopian troops,”
No one denies the fact that TFG is controlled and directed by TPLF, thus technically according to Kumalo’s report, 80% of the arms supplied to Al-shabab came from TPLF. Therefore, we should not be surprised when Ethiopia is supporting Al-shabab. The only thing we need to do is to find the reason why Ethiopia supports Al-shabab and other ethnic rebel groups in Somalia? Then, the answer becomes clearer. First, we need to understand TPLF’s method of operation. TPLF is like a wolf in sheep clothing. With its chameleon like long tongue always present itself to the west as an anti-terrorist regime. The United States and the international communities believed it. Not knowing TPLF’s tactical game behind the scene, with TPLF’s lead they all dipped their hands into the bowl of blood shed that they now regret. Eritrea’s continuous advocacy for an all-inclusive political solution for Somalia was refuted, and instead Eritrea was considered as a “spoiler”. Today, after a lot of try and error experiment, the international community realized that Ethiopia’s ill-advised strategy has created the worst humanitarian crisis in history, now it seems that the international community is prepared to change strategy so as to devise something functional to solve the Somalia issue. There is a saying that, “A man who carries a cat by the tail learns something he can learn in no other way”. Those who were stubborn to listen Eritrea’s advice for many years, now seems to embrace Eritrea’s strategic solution, which is an all-inclusive political participation of all parties for a peaceful and lasting solution for Somalia. By now, all parties have understood that every road to Somalia through TPLF is a crooked road and those who follow and walk along TPLF regime will see only crisis and destruction.
Because the international community has started to change strategy on Somalia, Eritrea went a step further by reactivating its IGAD membership to facilitate and pave the right way for Somalia’s political solution. TPLF’s strategy on Somalia seems like it is fading away and Eritrea’s innocent and genuine proposal solution for Somalia is gaining momentum and will soon take over the platform to lead the IGAD member states and the international community to a viable and lasting solution for Somalia’s crisis. TPLF is showing frustration as Eritrea joins IGAD because Eritrea’s strategic solution will bring all Somali parties into one table for a common benefit towards reconstituting Somalia. Ethiopia’s old and failed self-centered tactic of getting aid in the name of managing the Somalia crisis is vividly exposed that it is only intended to prolong TPLF’s life in power and today it is slowly loosing its popularity. TPLF’s paranoia is exposed with its silly and childish behavior at the IGAD council of ministers meeting in Addis Ababa on August 24th. TPLF’s security agents has abused, harassed and threatened Eritrea’s envoy and forcefully expelled Eritrea’s representative Biniam Berhe from the meeting. TPLF’s shameful frustration is a sign of weakness and defeat.
So, why is TPLF choosing instability and crisis as a means of survival to prolong its life expectancy in power? Let’s dig in to it more….
TPLF’s agenda in Somalia and its act of invasion in 2006 was not to fight terrorism but to disintegrate and weaken Somalia. Despite the clear evidence, Eritrea was instead used as a scape goat to conceal Ethiopia’s Evil adventurism. I wonder how many people know that Eritrea, even before it became a nation had been fighting against Bin laden and terrorism since 1989, this is even before the world knows Bin laden, but today, instead of acknowledging Eritrea’s contribution to world peace and security, the country was betrayed by the Security Council repeatedly and unfairly. In the world we live in today, reasonableness, fairness, impartiality and Justice has been continuously trodden underfoot, in its place arrogance and selfishness rules over righteousness. Like in the old times, “The innocent is convicted and Barabas the criminal was released” What a Justice!
Kumalo’s assertion of Ethiopia’s support to Al-shabab needs to be reconsidered. The regime in Ethiopia has managed to stay in power because of Al-Shabab. United States supported and protected TPLF both financially and politically, as a result, TPLF was saved from falling, thanks to its friend Al-shabab. The west has been misled, TPLF is not against Al-shabab, instead mysteriously encourages Al-shabab to remain functional .The Regime’s strategy on Somalia is a no peace and no war situation. To sustain this condition, Al-shabab is a concealed co-partner of TPLF. It is a well-known doctrine of TPLF that as long as Somalia is disintegrated and weakened, the regime’s life expectancy can be prolonged. That is why Ethiopia supplies arms both to the so called TFG and to Al-shabab mysteriously to keep the fire burning. In TPLF’s thinking, a stable Somalia is a threat to its survival. Here, we need some analysis and we should ask why it would cause a threat? Why is TPLF allergic to peace and stability? Well, in their reasoning, since they are a minority group, the only way to continue ruling is when there is disintegration and defragmentation in the region, on one hand easy for them to rule and on the other they get financial and political support in the name of fighting terrorism and managing the crisis.
The minority TPLF group represents 6% of Ethiopia’s 80 million population but controls close to 95% of the social, political and economic affairs of the country. What is more ironic however is, according to one reliable source, “93.5% of all key military positions in the Ethiopian National Defense Forces are occupied by ethnic Tigreans, far in excess of their 6% representation among the Ethiopian population”. So, what does this mean?. A united and integrated Somalia frightens TPLF, a united and strong Eritrea frustrates TPLF, and a united and cohesive Ethiopia terrorizes TPLF. This minority Regime is threatened by any sort of peace and stability. That is why it waged war with Eritrea and Somalia, because it feels uncomfortable to live in a stable and peaceful environment, that is why it chose the divide and rule policy by disuniting the people of Ethiopia in to different ethnic groups. Today, TPLF supports Al-Shabab because defragmented Somalia suites its way of thinking and governance. Therefore, as long as there is Al-shabab, TPLF can stay in power and extend its life expectancy.
This minority regime survives only when there is crisis and fragmentation in the region. Somalia’s disintegration benefits only TPLF. The United States and international community have been deceived and should reexamine TPLF agenda in Somalia. As long as this evil wolf is supported and allowed to continue its destabilizing mission in Somalia, there will be no peace in the Region.