May 2, 2013

እንደ ልጄ በሌሎች ዜጎች እየደረሰ ያለው ሰቆቃም ይቁም እላለሁ፡፡ ኣስገደ ገ/ስላሴ – መቐለ



የተከበራችሁ ሃገር ወዳጅ ዜጎች እኔ ህውሓትን በመቃወሜ፤ በተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ ተደራጅቼ በመታገሌ የህውሓት
የትግል ታሪክ ጋህዲ አንድ፣ ጋህዲ ሁለት እና ጋህዲ ሶስት እንዲሁም ሌሎች ፅሁፎች በመፃፌ በስም ማጥፋት ሰበብ ተከስሼ ለሁለት
ኣመት እየታሰርኩ እየተፈታሁ እስካሁን እየተንገላታሁ እንደምገኝ ሁሉም የሚያውቀው ነው፡፡
በጣም የሚያሳዝነኝ ግን የህውሓት ኢሃደግ ስርኣት መሪዎች የሚወስዱት እርምጃ ከወላጆቹ ኣልፎ ለልጅ የሚያልፍ ቂም
በቀል መስራታቸው ነው። የዚህ ልጅ መታሰር ከኣሁን በፊት ኣስረው የገረፉበት ምክንያት የኣስገደ ፀረ-መንግስት የሆኑ ፅህፎች
የምትሰራ ኣንተነህ በሚል እንደገረፉት ልጄ ራሱ የሚያረጋግጠው ነው፡፡
በመጨረሻ ልለው የምፈልገው ይህ ተግባር የሃገራችን በሚሊዮኖች ዜጎች መስዋእት የተረጋገጠ ህገመንግስት መናድና የህግ
የበላይነት ኣለመኖሩ በተጨባጭ ያረጋገጠ እኔ ስለ ልጄ ኣሁን በደረሰብኝ ችግር ብቻ ኣይደለም እየተናገርኩት ያለሁት በኣጠቃላይ ልክ
እንደ ልጄ በሌሎች ዜጎች እየደረሰ ያለው ሰቆቃም ይቁም እላለሁ፡፡

No comments:

Post a Comment