Mar 20, 2013

አራት አንጋፋ የህወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት በክብር ተሰናበቱ


ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አ.ማ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 11 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) ለቀናት ጉባኤውን ሲያካሂድ የሰነበተው የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ህወሃት በማጠናቀቂያው የፓርቲውን 45 የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ምርጫ እያካሄደ ይገኛል ።
ለዓመታት ፓርቲውን በማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ያገለገሉት አምባሳደር ስዩም መስፍን ፣ አምባሳደር ብርሃነ ገብረክርስቶስ ፣ አቶ አርከበ ዕቁባይና አቶ ዘርዓይ አስገዶም ባቀረቡት ጥያቄና ፓርቲው እየተገበረ ባለው የመተካካት ሂደት መሰረት በአዲስ አባላት እንዲተኩ የወሰነ ሲሆን አንጋፋ አባላቱ በክብር ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ተሰናብተዋል።
ላመንበት ዓላማ በመታገላችንና በመስራታችን አሁን ደግሞ በክብር በመሰናበታበታችን ክብር ይሰማናል ብለዋል አንጋፋ አባላቱ ።
የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ምርጫው ተካሂዶ የድምፅ ቆጠራ እየተከናወነ ይገኛል ።


Mar 19, 2013

የህወሃት/ኢህአዴግ የስለላ መረብ እየተበረበረ ነው ሰነዱን ምዕራባውያን፣ የስለላና የመብት ተቋማት ተርጉመውታል

የህወሃት/ኢህአዴግ የስለላ መረብ እየተበረበረ ነው
ሰነዱን ምዕራባውያን፣ የስለላና የመብት ተቋማት ተርጉመውታል
http://www.goolgule.com/tplf-eprdf-insa-is-under-watch/

“አዲሱ ቴሌ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ/ኢንሳ” በሚል ርዕስ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ያዘጋጀው ጥናታዊ ሪፖርት የታላላቅ አገር የስለላ ተቋማት፣ ለጉዳዩ አግባብ ያላቸው መምሪያዎችና የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ትኩረት መሳቡ ታወቀ። ሪፖርቱን አገራቱ በራሳቸው ቋንቋ በመተርጎም የህወሃት/ኢህአዴግን የስለላ መረብ ከተለያየ አቅጣጫ እየመረመሩት ነው።

የጎልጉል ምንጭ የሆኑ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው እንዳስታወቁት አኢጋን የህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም አዲሱ ቴሌን (ኢትዮ ቴሌኮምን) ከዋንኛው የስለላ መ/ቤት ብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት አገልግሎት በእንግሊዝኛው ምህጻረ ቃል NISS (National Intelligence and Security Service) እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ወይም በእንግሊዝኛው (Information Network Security Agency (INSA) – ኢንሳ) ጋር በማጋባት ስለላው በምን ዓይነት መልኩ እንደሚካሄድ በማመልከት ይፋ ያደረገው ባለ 47 ገጽ ሰነድ የተጠቀሱትን ክፍሎች ቀልብ የሳበው ዘገባው በወጣ ማግስት ነበር።

ሪፖርቱ ይፋ መደረጉን ተከትሎ የሪፖርቱ ባለቤት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዘገባውን ወደ እንግሊዝኛ በመቀየር ሰነዱን የሚጠቀሙ አካሎች እውቅና እንዲሰጡት ተጠይቆ እንደነበር ያስታወሱት የመረጃው ምንጭ፣ አኢጋን ተከታታይ ሪፖርቶችን የማዘጋጀት እቅድ እንዳለውና መረጃው በዋናነት ለኢትዮጵያዊ ወገኖች እንዲደርስ ታስቦ የተዘጋጀ በመሆኑ ለጊዜው የትርጉም ስራው ላይ ትኩረት እንደማያደርግ መግለጹን ተናግረዋል። ይሁንና አኢጋን ሪፖርቱን መጠቀም ለሚፈልጉና ተጨማሪ መረጃ ለሚፈልጉ ለመተባበር ዝግጁ መሆኑን በገለጸው መሰረት ሪፖርቱ ወደ ተለያዩ ቋንቋዎች ለመተርጎም በቅቷል።

ጀርመን፣ እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ካናዳ፣ እና ሌሎች የአውሮጳ መንግሥታ ሪፖርቱን ለራሳቸው ለመተርጎም ቅድሚያውን የያዙ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ኤምባሲ ካላቸው አገሮች መካከል ዋና የሚባሉት አስቀድሞ ከሚያደርጉት ጥንቃቄ በበለጠ ከስላለው መረብ ወጥመድ ውስጥ እንዳይወድቁ የማስጠንቀቂያ መመሪያ ከተላለፈላቸው ሰነባብቷል።

የደህንነቱን ስራ ከቴሌ ጋር በማገናኘት የተካኑትን የቻይና የቴሌኮም ኩባንያዎች በማስገባትና የአውሮፓን የቴሌኮም ተቋማትን “ወግዱ” በማለት ህወሃት/ኢህአዴግ እንዲሰናበቱ ማድረጉ ዋና ርዳታ ሰጪ አገሮችን ቅር አሰኝቷል። ከዚህም በላይ ከቴሌኮም ንግዱ ጎን ለጎን አገራቱን ከመረጃና ከአጋርነት ማግለሉ የፈጠረው ቅሬታ ቀን ጠብቆ የህወሃት/ኢህአዴግን አመራር ዋጋ እንደሚያስከፍለው የመረጃው ባለቤት ጨምረው ገልጸዋል።

የዓለም ታላላቅ አገሮችን ቀልብ የሳበውና ከፍተኛ መረጃዎችን የያዘው ሪፖርት በአገር ጉዳይ ላይ ትኩረት ሰጥተው በሚሰሩ የኅትመት፣ የድረገጽ፣ የድምጽና ምስል መገናኛዎች ሰፊ ሽፋን አለማግኘቱ የሪፖርቱን ባለቤት ብቻ ሳይሆን በትርጉሙ ላይ የተሳተፉትን አገራት የመረጃ ሰዎችን ያስገረመ ጉዳይ እንደነበር፣ ይሁንና በቅርቡ ሪፖርቱ ህይወት ዘርቶ በሁሉም ወገን እንደ ሰነድ የሚወሰድ እንደሚሆን የንቅናቄው የህዝብ ግንኙነት ክፍል ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በላከው የኢሜይል መልዕክት ተናግሯል። በመልዕክቱ ስማቸውን መዘርዘር ባያስፈልግም የተለያዩ የስለላ ድርጅቶችና አገሮች ሪፖርቱ በእንግሊዝኛ ተዘጋጅቶ እንዲሰጣቸው ጥያቄ አቅርበው እንደነበር ክፍሉ ገልጾዋል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ወይም በእንግሊዝኛው (Information Network Security Agency (INSA) አኢጋን ያወጣውን ሪፖርት ተከትሎ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት እለት ድረስ መቃወሚያም ሆነ ማስተባበያ አላቀረበም። ኢንሳ በቻይና የቴሌኮም ኩባንያ ዜድቲኢ አማካይነት የዜጎችን እንቅስቃሴ ወደ መረጃ ቋት ውስጥ በማስገባት የሚያካሂደው ስለላ፣ 


በተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችና አመራሮች ላይ እንዲሁም ኤምባሲዎች ላይ የሚያካሂደው ክትትልና በንጹሃን ላይ 

በሚፈጽመው አፈና በቅርቡ ይፋ የሚወጣ ከየአቅጣጫው ተቃውሞ ሊቀርብበት እንደሚችል ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ አመልክተዋል።

ኢህአዴግ በደቡብ ሱዳን የሚያካሂደውን ጣልቃ ገብነትና ጥቅምን የመጋራት “ወረራ” እና የህወሃት ወገን የሆኑ ነጋዴዎች በጁባ ስለሚያካሂዱት ስለላ አኢጋን በዝርዝር አቀርበዋለሁ ያለውን ተጨማሪ መረጃ አስመልክቶ በጥልቀት እየሰራበት መሆኑን ለጎልጉል አስታውቋል። መረጃውን መቼና እንዴት በምን ዓይነት መልኩ ይፋ እንደሚያደርግ ግን ቀን ቀጥሮ አላስታወቀም።

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ከአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ሕዝብ ግንኙነት ባገኘው ፈቃድ መሠረት “አዲሱ ቴሌና ኢንሳ፡ የህወሃት/ኢህአዴግ የስለላ መረብ” በሚል ርዕስ የወጣውን ዘገባ ከዚህ በታች አቅርበነዋል፡፡ አኢጋን በዘገባው ላይ በግልጽ እንዳስቀመጠው ጽሁፉን “ለማስተማሪነት፣ የቅስቀሳ ዘመቻ ለማካሄድ፣ ለጥናትና ምርምር እንደ ምንጭ በመጥቀስ ያለ ምንም ክፍያ መጠቀም ይቻላል፡፡”
“አዲሱ ቴሌ”
እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት
ኤጀንሲ (ኢንሳ)፡
የህወሃት/ኢህአዴግ የስለላ መረብ

ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ከሚያካሂዳቸው በርካታ ተግባራት በተጨማሪ ላለፉት ወራት የህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ያካሄደውንና ሊያካሂድ ያሰበውን የስለላ ተግባር ሲመረምር ቆይቷል፡፡ በተለይም ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም አዲሱ ቴሌን (ኢትዮ ቴሌኮምን) ከዋንኛው የስለላ መ/ቤት ብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት አገልግሎት በእንግሊዝኛው ምህጻረ ቃል NISS (National Intelligence and Security Service) እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ወይም በእንግሊዝኛው (Information Network Security Agency (INSA) – ኢንሳ ጋር በማጋባት ስለላውን በምን ዓይነት መልኩ ለማካሄድ እንዳሰበ የሚያትት ባለ 47 ገጽ ግርድፍ ዘገባ አቅርበናል፡፡

“አዲሱ ቴሌ” እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ (ኢንሳ)፡ የህወሃት/ኢህአዴግ የስለላ መረብ በሚል ርዕስ የቀረበው ይህ መረጃ በኢትዮጵያችን የተካሄደውንና በመካሄድ ላይ ያለውን የአፈና መዋቅር በጥቂቱ የሚያወሳ ነው። ዘገባው የህወሃት/ኢህአዴግ የደኅንነትና የአፈና ተቋማት ከቴሌኮም አገልግሎት ጋር እንዴትና ለምን እንደተቆራኙ፣ የምዕራብ አገራት የቴሌኮም ቴክኖሎጂ የተገፋበትን ምስጢር፣ አዲሱን ቴሌ ከአገር ወዳዶች በማጽዳት የህወሃት/ኢህአዴግን ፖለቲካና ስውር አጀንዳ ማስፈጸም ይችላሉ ተብለው ለታመነባቸው ክፍሎች ወይም የአገዛዙ “ቁሶች” እንዲዛወር የተደረገበትን ምክንያት፣ በፖለቲካ ድርጅቶችንና ኃላፊዎች እንዲሁም መንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች (መያዶች) ላይ የሚካሄደውን ስለላ በመጠኑ ለማሳየት ጥረት ተደርጓል፡፡

በመጨረሻም ይህንን የስለላ መረብ በመጣስ ሕዝባችን ትግሉን በምን ዓይነት መልኩ ማከናወን እንዳለበትና እንዴት የመረጃ ጫካ ውስጥ በመግባት መደበቅ እንደሚቻል የተወሰኑ ሃሳቦችን ለመዳሰስ ተሞክሯል፡፡

በባህርዳር ጊዮን ሆቴል ጉዳይ የተነሳ የአማራ ክልል ባለስልጣናትና ህወሀት ተፋጠዋል


የዛሬ 21 አመት ህወሀት/ ኢህአዴግ አሸንፎ አዲስ አበባን ከመቆጣጠሩ በፊት ለህወሀት በመሰለል ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረጋቸው የሚታወቁት በባህርዳር ከተማ ነዋሪ የሆኑት የአድዋው ተወላጅ እና የአቶ መለስ ዜናዊ የቅርብ ዘመድ አቶ ወልዱ፣ ለህወሀት  ላበረከቱት አስተዋጽኦ ፣ አቶ መለስ ዜናዊ የመንግስት ንብረት የሆነውን ጊዮን ሄቴልን በ5 ሺ ብር ኪራይ እንዲሰሩበት በገጸ በረከት ስጥተዋቸው ነበር።

አቶ ወልዱ በልጃቸው በአቶ ብስራት ወልዱ ዋና አስተዳዳሪነት ሆቴሉን ሲሰሩበት እና ከፍተኛ ግብር ሲያጋብሱበት ከቆዩ በሁዋላ፣ ህዝቡ በባህርዳር ከተማ አንድ ኪዎስክ በ5 ሺ ብር እየተከራየ ጊዮን ሆቴልን የሚያክል በስፋቱና በጥራቱ ተወዳዳሪ የሌለውን ሆቴል እንዴት መንግስት በ5 ሺ ብር ያከራያል በማለት ተቃውሞ ሲያሰማ መቆየቱን ተከትሎ፣ የፌደራል የኪራይ ቤቶች ድርጅት የክልሉ መንግስት ቤቶች ኤጀንሲ ሆቴሉን እንዲረከብ ለአማራ ክልል ቤቶች አስተዳዳር አምና ደብዳቤ ጽፏል።
ሆቴሉን እንዲያስረክቡ ድብዳቤ የደረሳቸው አቶ ወልዱ  በቀጥታ ለአቶ በረከት ፣ ለፌዴሩሽን ምክር ቤት ሰብሳቢው ለአቶ ካሳ ተክለብርሀንና ለቀድሞው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አዲሱ ለገሰ ፣ የብሄር ብሄረሰቦችን በአል ለማክበር አዲስ አበባ በተገኙበት ወቅት፣ አቶ መለስ ዜናዊ መሞታቸውን ተክትሎ ቤቱን እንዲያስረክቡ መጠየቃቸውን በመናገራቸው፣ ባለስልጣኖቹ የክልሉ መንግስት የጻፈውን ደብዳቤ እንዲያነሳ መጠየቃቸው ታውቋል።
የክልሉ ቤቶች ኤጀንሲ ጉዳዩ ከፍተኛ ዝርፊያ መሆኑን ቢገልጽም፣ የሆቴሉ አስተዳዳሪ የአቶ ወልዱ ልጅ ብስራት ወልዱ የክልሉን ባለስልጣናት በማስፈራራት እርምጃ እንደሚወስድ በመዛት ሆቴሉን ለማስረከብ ፈቃደኛ እንደማይሆን በመግለጹ ክልሉ የሚያደርገው ጠፍቶት ተቀምጧል። የከተማው ህዝብ በበኩሉ የክልላችንን ባለስልጣኖች አንድ የህወሀት አባል ሰው እንደልቡ እያሽከረከራቸው  በማለት ትችት እያቀረበ ነው። ህዝቡ በተደጋጋሚ የሆቴሉን ጉዳይ አንድ እልባት እንዲሰጠው እየጠየቀ ቢሆንም፣ የክልሉ ባለስልጣናት ምንም ማድረግ እንደማይችሉ እያስታወቁ ነው።
የጊዎን ሆቴል በጣና ዳር የተሰራ በርካታ አልጋዎችን በቀን ከ175 እስከ 250 ብር በሚደርስ ዋጋ ለቱሪስቶች የሚያከራይ፣ የአገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ወደ ሆቴሉ ሲሄዱ በነጻ የሚስተናገዱበት፣ በውስጡ የያዘው ቡናና ፍራፍሬ ከፍተኛ ገቢ የሚያስገኙ ዘመናዊ ሄቴል ነው። የድርጅቱ የቀን ገቢ በ10 ሺዎች የሚቆጠር ቢሆንም ፣ ባለሀብቱ በወር የሚከፍሉት የኪራይ መጠን 5 ሺ ብር ብቻ ነው። ጭቅጭቅ ከተነሳበት ከአምና ጀምሮ ደግሞ ባለሀብቱ የአምስት ሺ ብር የቤት ኪራይ መክፈል ማቆማቸው ታውቋል።
ከምንም የተነሱት የሆቴሉ ባለቤት ከ21 አመታት በሁዋላ እጅግ የናጠጡ ሀብታም ለመሆንና የተለያዩ ድርጅቶችንም ለመክፈት ችለዋል።
ጉዳዩን በማስመልከት ጥያቄ ያቀረብንለት አንድ የኪራይ ቤቶች ድርጅት ሰራተኛ ” ግለሰቡ ቤቱን እንዲያስረክቡ ሲጻፍላቸው ዋጋህን ታገኛለህ” የሚል መልስ መስጠታቸውን ገልጿል። የክልሉ መንግስት እየደረሰበት ካለው ትችት ነጻ መሆን የሚችለው ግለሰቡ ሆቴሉን እንዲያስረክቡ ሲያደርግ እና እንደማንኛውም ሰው ተጫርተው ተገቢውን ክፍያ መክፈል ሲችሉ ብቻ ነው” ብሎአል።
አንድ ሌላ የባህርዳር ነዋሪ ደግሞ  ጊዮን ሄቴል ህወሀት በክልላችን ያለውን የበላይነት ለማሳየት ጥሩ ምሳሌ ነው ብሎአል።
በጉዳዩ ዙሪያ የሆቴሉን ባለቤትም ሆነ የክልሉን መንግስት ለማግኘት ያደርገው መኩራ አልተሳካም። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚታየው የአንድ ዘር የኢኮኖሚ፣ ወታደራዊና ፖለቲካዊ የበላይነት የአገሪቱ መነጋጋሪያ እየሆነ መምጣቱን መዘገባችን ይታወሳል።
source: ኢሳት ዜና: 

The following is from his blog

The Boss of Bahir Dar: Bisrat at the Ghion Hotel

If you need to get anything arranged in Bahir Dar, go and see Bisrat at the Ghion Hotel. He is a fabulous man who manages the Ghion Hotel (a budget hotel with a beautiful lakeside patio and a wonderful, relaxed vibe). Even though we did not stay at the Ghion (it is an older hotel in need of some renos), Bisrat arranged our tour to the Blue Nile falls and organized our trip back to Addis (the Ghion tours to the Blue Nile Falls are listed in the Lonely Planet). Our discovery of Ato Bisrat was a wonderful side-benefit of visiting the Ghion.

When we called and complained about our shady mini-bus driver (Iago), Bisrat took immediate action and said he would handle the situation, promising even to return our deposit. Bisrat is one of those people you meet in life that goes out of his way to help you even if he does not have to. He did not gain by helping us (in fact he might still have to endure the drama associated with Iago), but he helped us just the same. If you visit Bahir Dar and you should (it is stunning), call Bisrat. He will help you out. Who’s the Boss in Bahir Dar? No, not Tony Danza or Judith Light. It’s Bisrat.

from American observer 

   I keep thinking I should be coming up with deep thoughts and Truths about what being in Africa is about, but I’ve only been here a week or so and am still feeling my way. But what about this: at the Ghion Hotel I proofread and edited some documents for Bisrat, the manager in exchange for a hot shower in his office and a discount on a boat trip the next morning—and I don’t even stay at the Ghion!
     The point is to have the liberating feeling that anything is possible. Tomorrow I may feel the opposite, but just to have the feeling, however fleeting it may prove to be, makes being here exciting.     
                                                                                                   Doesn't Bisrat look like Charles Barkley?


     Everyone gravitates to the Ghion. It has an ideal, relaxed setting next to Lake Tana, good food, cold drinks, soothing breezes and horrendous mosquitoes at dusk. Bisrat is a fixer, able to arrange everything you could need: transport, hotels, tours, communications, etc. I like him because he not only looks like Charles Barkley, especially when he raises his eyebrows, but he has a sense of humor that I like.
     He had an employment poster for a new hotel opening in Addis Ababa and I said he shouldn’t show it to his staff or they might leave. Without missing a beat, he deadpanned, “I hope they leave.”
     He made a call for me to a hotel in the next town I am going. While on the line he said to me, “They’re full.” As a joke I said, “Tell them I’m American.”
     In an authoritarian voice he barked into the phone, “He’s American!” and then with professional comic timing, “Hello?” faking that they hung up on him.
  

ጄኔራል ግራዚያኒን ኃውልት ግንባታ ተቃዉመዉ ከታሰሩት ሰልፈኞች አንደበት

ቀይ ለባሾቹ ሰልፈኞች የታጎሩት በአራዳ ፖሊስ መምሪያ ጊቢ ውስጥ ነበር

(በበፍቃዱ ኃይሉ)
EMF – መጋቢት 8/2005 የባለራዕይ ወጣቶች ማኅበር እና የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የኢትዮጵያውያን ጠላት የነበረው የፋሺስት ጣሊያን ጄኔራል ግራዚያኒን ኃውልት (በጣሊያን አገር፣ የትውልድ መንደሩ አካባቢ) መቆም በመቃወም የሰልፍ ጉዞ ከስድስት ኪሎ (የካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ ኀውልት) እስከ ጣሊያን ኤምባሲ ድረስ ለማድረግ እየተንቀሳቀሱ ነበር፡፡ የሰልፉ ተሳታፊዎች ከጀርባው ላይ ‹‹ለግራዚያኒ ኀውልት ማሠራት አባቶቻችን የከፈሉትን መስዋዕትነት ማራከስ ነው›› የሚል ጽሑፍ የታተመበት ቀይ ቲ-ሸርት ለብሰው ነበር፡፡ የኢሕአዴግ ካድሬዎች ደግሞ ‹‹ይቺ ባቄላ…›› በሚል ምክንያት ነው መሰለኝ ‹‹የተቃውሞ ሰልፍ…›› የሚባለውን ነገር ለማስቆም ራሱ ግብግብ ፈጠረ፣ ወጣቷ ዓለምን የቀን አጋጣሚ ስድስት ኪሎ አካባቢ፣ በዕለተ እሁድ (መጋቢት 8/2005) አንቀዥቅዦ አመጣት፡፡ የለበሰችው የአዘቦት ቀይ ቲ-ሸርት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ለመዋል ምክንያት ይሆነኛል ብላ አልተገመተችም ነበር፡፡ ፌዴራል ፖሊስ ቀይ ለባሾቹን ማፈስ ሲጀምር ዓለምንም አብሮ አፍሶ አጋዛት፡፡
ቀይ ለባሾቹ ሰልፈኞች የታጎሩት በአራዳ ፖሊስ መምሪያ ጊቢ ውስጥ ነበር

በተመሳሳይ ሰዓት ለሥራ ጉዳይ ጓዙን ጠቅልሎ ወደአፋር ለመጓዝ እየጠበቁት ያሉ ባልደረቦቹን ለማግኘት በታክሲ ውስጥ ይጓዝ የነበረ አንድ ሰው ከስድስት ኪሎ ተነስቶ አምስት ኪሎ እስኪደርስ የተመለከተውን ሁካታ ዓይቶ ላለማለፍ ከታክሲ ይወርዳል፡፡ ፖሊሶች ከሰልፈኞቹ ውስጥ አሳደው የያዙትን እያፈሱ መኪና ውስጥ ሲያጉሩ፣ ከፖሊሶች ዕይታ እየተሰወረ በሞባይሉ ፎቶ ለማንሳት ሲሞክር፣ አንድም የረባ ፎቶ ሳያነሳ በሦስተኛው ፎቶ ላይ ከፖሊሶች ጋር ዓይን ለዓይን ተጋጠመ፡፡ እሱም ተይዞ ተከተላቸው፡፡ ይህ ድንገተኛ እስረኛ የዚህ ጽሑፍ ጸሐፊ ሆነ፡፡
የታፈሱት ሰልፈኞች ሁሉ የታጎሩት በአራዳ ፖሊስ መምሪያ ጊቢ ውስጥ ነበር፡፡ ጊቢው ውስጥ እንደደረስኩ ከፊት ለፊቴ ደረጃው ላይ የተኮለኮሉትን ሰልፈኞች ተመለከትኩ፡፡ ወጣቶቹ ታፍሰው የገቡ ሳይሆን ወደው የተሰበሰቡ ይመስሉ ነበር፡፡ እንዲያውም በገባሁ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ጮክ ብለው ይዘፍኑ ጀመር፡-
‹‹… ተከብረሽ የኖርሽው ባባቶቻችን ደም፣ ባባቶቻችን ደም
እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም…››
በዚህ ጊዜ ከፖሊሶቹ አንዱ አብሮ ሲዘምር ይታይ ነበር፡፡ ፖሊሶቹ የተሻለ ትሁቶች ቢሆኑም፣ ሲቪል ለባሾቹ ግን ማመናጨቅ እና ማዋከብ ዋነኛ ሥራቸው ነበር፡፡ እኔን በመኪና ይዘውኝ ከመጡት ውስጥ አንዱ ‹‹ዴሞክራሲ በዛ…›› የሚለውን ቃል እየደጋገመ በቁጭት ይናገራል፡፡ ብዙዎቹ የመምሪያው ፖሊሶች ከየት እንደመጣ የማያውቁት ኮማንደር ግን የተቆጨው በመዘግየቱ ነው፤ ‹‹ይሄን ያክል እስኪሰባሰቡ መቆየት አልነበረብንም›› አለ – እኔው ጎን ቁጭ ብለው ሲነጋገሩ፡፡ በሬዲዮናቸው ሲለዋወጡ ከነበረው ውስጥም ‹‹ሱማሌ ተራ የተጎዳውን ሰውዬ የት ወሰዳችሁት?… ተክለሃይማኖት ሆስፒታል?…›› ይባባሉ ነበር፡፡ በዚሁ ጉዳይ ይሁን አይሁን ግን ‹‹መረጃም (ማስረጃም)›› አልነበረኝም፡፡
ጊቢው ውስጥ ከሌሎቹ እንዳልቀላቀልና ብቻዬን እንድቆይ አድርገውኛል፡፡ ባንድ በኩል ስልኬ ላይ ያሉትን ፎቶዎች አጥፍተው ይፈቱኛል፣ ጉዞዬም ይቀጥላል በሚል ደስ ብሎኛል፡፡ በሌላ በኩል በዓይን የማውቃቸውን እነዚያን ልጆች ቀረብ ብዬ አለማነጋገሬ ቆጭቶኛል፡፡ በዚህ መሐል ግን ሁሉም እየሄዱ ቃል ሲሰጡ ቆዩ (ቃል ሲባል ቃል እንዳይመስላችሁ፤ ከስም አንስቶ የኔ የምትሉትን ነገር በሙሉ ይጠይቋችኋል)፤ ከዚያም የኔም ተራ ደረሰና ቃል ሰጥቼ ሳበቃ እኔም በቀላሉ እንደማልሰናበት ሲያረዱኝ የጓዝ ኮተቴን ሁሉ አስመዝግቤ እዚያው ተጠቃለልኩ፡፡
ከዚያም ቃል የመስጠቱ ሥነ ስርዓት ቀጠለ፤ የመጣው ሁሉ በራሱ መንገድ ያንኑ ጥያቄ መልሶ፣ መላልሶ እያንዳንዱን ታሳሪ (ተጠርጣሪ ልበል ይሆን?) ይጠይቃል፤ እያንዳንዱም ተጠርጣሪ ይመልሳል፡፡ ሆኖም ብዙዎቹን መርማሪዎች የብስጭት መንስኤ የሚሆን ነገር ባለራዕዮቹ ወጣቶች ሳይናገሩ አይወጡም ነበር፡፡ ብሔር ሲባሉ ‹‹ኢትዮጵያዊ›› ይላሉ፡፡ ይህንን የሚሉት ‹‹ብሔር›› የሚለው ቃል ከግዕዝ የተወሰደ ሲሆን፣ ትርጉሙም ‹‹አገር›› መሆኑን እያጣቀሱ ነው፡፡ ታዲያ ይህ አባባል ለመርማሪዎቹ የሚያበሳጭ ድፍረት ነበር፡፡
ፖሊሶቹ የሆነችውን ሁሉ እየደወሉ፣ ለአለቆቻቸው ይናገራሉ፡፡ ከዚህ መሐል ከሰልፈኞቹ አንዱ ለብሶት የነበረው ባንዲራ ላይ በእስክርቢቶ የጻፈውን ደብዳቤ ከስልኩ ወዲያ ላለ ሰው በንባብ ሲያጽፉት ሰምቻለሁ፡፡ ጽሑፉ ባብዛኛው መንፈሳዊ ነው ቢባል ይቀላል፡፡ ‹‹ለእመቤታችን በአስራትነት የተሰጠችው አገራችን ኢትዮጵያ…›› ብሎ ነው የሚጀምረው፡፡
ምርመራው/ጥያቄው ቀጥሏል፤ ከጠያቂዎቹ መካከል የደኅንነት እና የኢንሳ ሰዎችም ነበሩበት፡፡ ከጥያቄዎቻቸውም ውስጥ የኢሜይል አድራሻ እና የይለፍ ቃል፣ የፌስቡክ አድራሻ እና የይለፍ ቃልም ይጠይቁ ነበር፡፡ እያንዳንዱ ታሳሪ (ተጠርጣሪ አልልም) ስሙን በቪድዮ ካሜራ ፊት እንዲናገር ይገደድ ነበር፡፡ እንግዲህ ይህንኛው መጀመሪያ ላይ እያንዳንዱ ሰው ከተነሳው ፎቶ በተጨማሪ መሆኑ ነው፡፡ በዚህ የጅምላ እስር ውስጥ ካስተዋልኳቸው ጉዳዮች ውስጥ የሴቶቻችንን ጀግንነት ነበር፡፡ ለምሳሌ፣ እኔ ያለምንም ማንገራገር ምስሌን አስቀርጬ ወደቃለመጠይቁ ሳልፍ የሰማያዊ ፓርቲዋ አመራር አባል ሐና ዋለልኝ ‹‹አልቀረጽም፣ አሻፈረኝ›› ብላ ስትሟገት ድምፅዋ ይሰማኝ ነበር፡፡
ሲመሽ ይፈቱን ይሆን? እዚሁ ያሳድሩን ይሆን? ሌላ ቦታ ይወስዱን ይሆን? ምን ብለው ይከሱን ይሆን? እየተባባልን የተሰባሰብንባት አንዲት በረንዳ መሳይ ክፍል ውስጥ፣ ኢቴቪ በቀጥታ የሚያስተላልፋቸውን የአዳማ እና የመቐለ የኦሕዴድ እና የሕወሓት ስብሰባዎች መኮምኮም ጀመርን፡፡ አሳሪዎቻችንም በስልክ አለቆቻቸውን እያነጋገሩ ሽር ጉዳቸውን አጧጡፈውታል፡፡ ኢቴቪም ብቻውን በዓሉን ማክበር አልቻለም፡፡ መብራቱ ብልጭ ድርግም አበዛ፡፡ ብልጭ ድርግም አልኩ እንጂ ያበዛውስ ድርግም ማለት ነው፤ አልፎ፣ አልፎ ግን ላፍታ ብልጭ እያለ ነበር፡፡ በጨለማው ውስጥ ራታችንን በጨለማ ተቋደስን፡፡ ሁላችንም ምሳ ያልበላን ቢሆንም አንዳንዶች ግን ቁርሳቸውንም አልበሉም፡፡
የመታሰራችን ዜና በማኅበራዊ አውታሮች በመጠኑ ቢስተገባም የብዙዎቻችን ቤተሰቦች ግን አልሰሙም፤ ደውሎ የማሳወቅ ዕድሉም አልተሰጠንም፡፡ እዚያው ጨለማ ውስጥ ከቆየን በኋላ ወደ 3፡00 ሰዓት ገደማ ወደ ጃንሜዳ አካባቢ የሚገኝ ማረሚያ (እስር ቤት) በሁለት ዙር ተወሰድን ከ30 በላይ እስረኞች አንድ ላስቲክ ብቻ ወለሉ ላይ የተነጠፈበት ክፍል ውስጥ ብንታጎርም በእርስ በርሳችን ጫወታ ተጠምደን ነበር፡፡ (በነገራችን ላይ እኛ ወደዚህ እስር ቤት ስንዛወር ቀይ ለባሽዋ ዓለም ተለቅቃ ወደቤቷ ሄዳለች፡፡) የሄድንበት በሰልፉ ዋዜማ ሲቀሰቅሱ ከታሰሩ ሌሎች ጋር ተቀላቅለናል፡፡ የጅምላ እስሩ ጉዳይ በዋዜማው እንደተጀመረ ያወቅኩትም ያኔ ነው፡፡ ቀድመው ከታሰሩት ውስጥ ሁለቱ ክፉኛ ቡጢ እና ካልቾ ቀምሰው እንደሆነ ለማወቅ እስኪናገሩ መጠበቅ አያስፈልገንም ነበር፤ የአንደኛው ጃኬት የደረቀ ደም ከፊትለፊት ይታይበታል፡፡
ለአምስት ሰዓት ዐሥራ አምስት ደቂቃዎች ሲቀሩት ግን እንደገና እንድንንቀሳቀስ ተነገረን፡፡ ከኛ ቀደም ብለው ሴቶቹም ወደቀጨኔ (ችሎት መድኃኔዓለም ኮንዴሚኒዬም አጠገበ ያለ) ወረዳ 9 ማረሚያ ቤት እንደተወሰዱ እና ከኛም ውስጥ 12ቶቻችን መከተል እንዳለብን ተነገረን፡፡ እዚያ እንደደረስን ግን ምነው እዚያው በቀረን የሚያስብል ትዕይንት ገጠመን፡፡ እያንዳንዱ ክፍል እላይ በላይ ተደራርበው በተኙ እስረኞች ተጨናንቋል፡፡ ሌላው ቀርቶ ጫማ ማስቀመጫ ቦታ እንኳን በክፍሉ ውስጥ ስለሌለ ጫማዎቻችንን ውጪ እያስቀመጥን እንድንገባ ተገደድን፡፡ ሦስቱ (አራት ሜትር በአራት ሜትር የሚገመቱ) ክፍሎች ውስጥ አንዱ 37፣ አንዱ 34 እና ሌላኛው ውስጥ 30 እስረኞችን ይዟል፡፡
እንዳጋጣሚ 30 ሰዎች የያዘው ውስጥ ነበር እኔ የደረሰኝ፡፡ የኛ ክፍል ይሻላል ተብሎ ዶ/ር ያዕቆብንም አመጧቸው፡፡ ጉዳዩ በጣም አሳዛኝ ነበር፡፡ እኛስ ባልደከመ ጉልበታችን እንችለዋለን፤ ለርሳቸው ግን በጣም ፈታኝ እንደሚሆን መገመት ቀላል ነው፡፡ ክፍሉ በጣም ጥቅጥቅ ብሎ ከመሞላቱ የተነሳ ለኛ ቦታ ለማግኘት የቤቱ ካቦ ተነስቶ እያንዳንዱን እስረኛ እየቀሰቀሰ ማጠጋጋት ነበረበት፡፡ በቦታ ጥበት ምክንያት ደረቁ ወለል ላይ በአንድ ጎናችን እንድንተኛ ከመገደዳችን የተነሳ እኔ ይህን ጽሑፍ እስከምጽፍበት ሰዓት ድረስ ቁርቋሬው የፈጠረው ሕመም ጎኔን አያስነካኝም፡፡ ካቦው አጠጋግቶልን ሲጨርስ ሁላችንንም የገቢ ገንዘብ ተቀበለን እና ተኛን፡፡ እዚያ ክፍል ውስጥ መተኛት ማለት፣ መተኛት ማለት አይደለም፡፡ የክፍሉ መታፈን እና አስቀያሚ ጠረን፣ ሙቀት፣ በዚያ ላይ እየተቀባበሉ የሚያጨሱት ሲጃራ ጢስ፣ ከዚያ እና ከዚህ የሚተኮስ የፈስ ሽታ… ብቻ የአበሳ ናሙና ነበር፡፡ ሌሊቱን ሲዘንብ ማደሩ ግን በከፊልም ቢሆን የክፍሉን አየር አቀዝቅዞታል፤ ችግሩ ዝናቡ ውጪ ያስቀመጥነው ጫማ ውስጥ ውኃ መሙላቱ ብቻ ነበር፡፡
እንደምንም ነጋልንና ወደፍርድ ቤት እንደምንሄድ ተነግሮን ጥንድ ጥንድ እየተደረግ በካቴና ተቆላለፍን፡፡ ከመሐከላችን አንዱ የማኅበሩ አባል፣ ፀጉሩን አጎፍሮ ስለነበር (ለፍርድ ቤቱ ውበት አይመጥንም ብለው ይሆናል) ይቆረጥ አሉና መቀስ አንስተው ይከመክሙት ጀመር፡፡ ፀጉሩን ቆርጠው ሲጨርሱ አሰለፉንና ካቴናችንን ፈቱት፡፡ ‹‹ፍርድ ቤት መወሰዳችሁ ቀርቷል፣ ምናልባት ፖሊስ ጉዳዩን ይፈታዋል›› ተባልንና ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ወደጃንሜዳ ማረሚያ ቤት መልሰው ወሰዱን፡፡ እዚያ ስንደርስ ለፖሊስ ዋስ እያቀረብን እንድንፈታ ተፈቀደልን፡፡ ቀድሞውንም የታሰርነው ያለወንጀል በመሆኑ አስገራሚ ውለታ አልነበረም፡፡
የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ የሚያስፈልገው ቅድመ ሁኔታ ለመስተዳድሩ ማሳወቅ ሲሆን፣ መስተዳድሩ ደግሞ በ24 ሰዓት ውስጥ ‹‹አይሆንም›› የሚል ደብዳቤ ካልጻፈ እንደተፈቀደ ይቆጠራል፡፡ ስለዚህ ሰልፍ ማድረጉ ሕጋዊ ስህተት የለበትም፣ ጉዳዩ ባንድ ጀምበር የተወለደ ሳይሆን ጋዜጦች ዜና የሰሩለት፣ ቁጥቦቹ ሬድዮዎች ሳይቀሩ ያወሩለት ጉዳይ ስለሆነ ወንጀል ነው ፍርድ ቤት ሊያቀርቡት አይችሉም/አይገባቸውምም፡፡ ነገር ግን ‹‹…ካፈርኩ አይመልሰኝ…›› ይመስላል በዋስትና እንድንፈታ ፈቅደው ያገቱብንን ንብረቶቻችንን እየመለሱ መጋቢት 9/2005 እኩለ ቀን ላይ አሰናበቱን፡፡

Mar 18, 2013

“ለምንድነው የኢትዮዽያ የፖለቲካ ድርጅቶች እንደኣሸን የሚፈሉ?”


‎! …….. የኢትዮዽያ ፖለቲከኞች ………!
ጥያቄ , “ለምንድነው የኢትዮዽያ የፖለቲካ ድርጅቶች እንደኣሸን የሚፈሉ?”
በኢትዮዽያ የፖለቲካ ድርጅቶች (ፓርቲዎች) ኣመሰራረት ርእዮተ ዓለም (Ideology) ወይ ሳይንሳዊ መርህ መሰረት (Principle based) ያደረገ ሳይሆን በዘረኝነት ወይ ጎሰኝነትና ጎጠኝነት የተቃኘ በመሆኑ ነው። የዚ ሁሉ ምክንያት ምንድነው?
1) የማህበረሰቡ የፖለቲካ ንቃተ ህሊና ማነስ ነው። በኢትዮዽያ መርህ መሰረት ያደረገ ፖለቲካ ማራመድ የህዝብ ድጋፍ ኣያስገኝም። የፖለቲካ rationality የለም። ድጋፍ ለማግኘት የጎሰኝነትና ጎጠኝነት ቅስቀሳዎች ጠቃሚ ናቸው። ‘እንደዚህ ተበደልን፣ እንዲህ ኣረጉን …’ ስትል የህዝቡን ስሜት (ወይ ቀልብ) መግዛት ትችላለህ። የተለያየ ጎሳና ጎጥ የተለያየ ፓርቲ ያመርታል። ለምሳሌ ህወሓት ድጋፍ የሚሰበስበውና ስልጣን የያዘው በዚ መንገድ ነው።
2) የኣብዛኞቹ ፖለቲከኞች ዋና ዓላማ ስልጣን መሆኑ ነው (ስልጣን መያዝና መሪ ሁኖ መከበር በቃ)። ለዚህም ጥሩ ኣማራጭ የየራሳቸው ፓርቲ በመመስረት የፓርቲው ሊቀመንበር (ፕረዚደንት) መሆን ያምራቸዋል። ለዚህም ነው በሀገራችን እነዚህ “33 የተቃዋሚ ፓርቲዎች “ የሚባሉ ጨምሮ ከ60 በላይ ፓርቲዎች ኣሉ የሚባለው።
3) የገዢው ፓርቲ ሴራዎች:: ህወሓት/ኢህኣዴግ ጥሩ ነገር በመስራት ተቃዋሚዎችን ለማሸነፍ ከመሞከር ይልቅ የመንግስትን ሃብትና መዋቅር በመጠቀም ተቃናቃኞችን በማፍረስና ማዳከም ሴራ መጠመዱ ሌላው ምክንያት ነው። በሚያደርገው በስለላ የተደገፈ conspiracy የተቃዋሚ መሪዎች (የገዢው ፓርቲ የጥፋት ስራ መሆኑ ስለማይገነዘቡ) እርስበርሳቸው እንዳይተማመኑና ኣንድነት እንዳይፈጥሩ ስለሚያደርግ ነው።
4) የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሳሳተ የትግል ኣቅጣጫ (Game Theory)። ኣንዳንድ ፖለቲከኞች (እንዳውም ኣብዛኞቹ) የህዝብን ስሜት ለመግዛት ሲባል ዘረኝነትን የሚቃወሙ እየመሰሉ በተግባር ግን ራሳቸው ዘረኝነትን (ጎሰኝነትን) ያጠቃቸዋል። እንደውጤትም ሁሉም ዘረኛ ሁነው ይገኛሉ። ሌሎች ከነሱ ጋ ከመቀላቀል ይልቅ ከነሱ ራሳቸው ለመከላከል ሲሉ ሌላ ድርጅት መመስረት ይፈልጋሉ። ፓርቲዎችም ይበዛሉ።
ለምሳሌ
(ሀ) ኣንዳንድ ዘረኝነት ወይ ጎሰኝነትን እንቃወማለን፣ በዘር መከፋፈል ይቅር እያሉ የሚሰብኩ ኋይሎች ግንቦት -7 ከዴምህት (ዴሞክራሲያዊ ምንቅስቃስ ህዝቢ ትግራይ ወይ የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ) ኣብሮ እየተንቀሳቀሰ ነው ብለው ይከሳሉ (ይወቅሳሉ)። ይሄ ፓርቲዎች በዘር ተከፋፍለው እንዲቀሩ ያደርጋል።
(ለ) ህወሓት/ኢህኣዴግ በራሱ ጎጠኝነትን እቃወማለሁ እያለ “ዓረና ትግራይ ፓርቲ ከጠላቶቻችን ሸዋ ፖለቲከኞች በማበር የትግራይን ህዝብ ለመግደል እየተንቀሳቀሰ ነው “ በሚል ስም ያጠፋል። ታድያ ዓረና ፓርቲ ኮ ትግራይ የመገንጠል ዓላማ የለውም፤ ከሌሎች የኢትዮዽያ እህት ፓርቲዎች ይሰራል እንጂ ለብቻው መሆንኮ ኣይደገፍም። ኣብሮነት ጥሩ ነው። ዙሮዙሮ ግን ይሄም ፓርቲዎች እንዳያብሩ ምክንያት ይፈጥራል።
(ሐ) ሰመያዊ ፓርቲ የመሰረቱ ፖለቲከኞች (እንደሚባለው) የኢትዮዽያ ኣንድነት ይሰብካሉ። ዘር ወይ ጎሳ መሰረት ያደረገ ፓርቲ እንደማይደግፉም ይነገራል። እነዚህ ሰዎች ታድያ (የሰማሁት ትክክል ከሆነ ምክንያቱም እንደዚህ ዓይነት ኣስተሳሰብ ከፖለቲከኛ ኣይጠበቅም) የኣንድነት ፓርቲ ኣባላት የነበሩ ሲሆን ፓርቲው (ኣንድነት) እነሱ የማይፈልጉዋቸውን ሰዎች (እነ ስየ ኣብርሃ የትግራይ ተወላጆችን በኣባልነት ስለያዘ) ከፓርቲው ለቀው በመውጣት “ኣዲሱ”ን ሰማያዊ ፓርቲ መሰረቱ። (የፓርቲዎች ቁጥር ጨመረ)።
ይህንን መረጃ (ምሳሌ ‘ሐ’) ትክክል ከሆነ ማለትም ሰመያዊ ፓርቲ ከሌሎች ብሄሮች (ለምሳሌ ትግራይ) በኣባልነት ካልተቀበለ መጨረሻው ምን ሊሆን ነው? እንበልና ሰማያዊ ፓርቲ ስልጣን ያዘ (የኣንድ ፓርቲ ዓላማ ስልጣን መያዝ ስለሆነ) ከዛ እንዴት ኣድርጎ ሀገርን ያስተዳድራል? ወይስ ኣማራ ክልልና ኣዲስ ኣባባ ብቻ ገንጥሎ ሀገር ሊመሰርት ነው?
ጎሰኝነት ወይ ዘረኝነት ኣንቀበልም ስንል ከተለያዩ ብሄሮች በኣባልነት ኣንቀበልም ማለት ሊሆን ኣይገባውም። በኣጭሩ በኢትዮዽያ ፓርቲዎች እንደ ኣሸን የሚፈሉ ገዢ የሆነ ርእዮተ ዓለም መሰረት ያደረገ የፓርቲ ስርዓት ስለሌለ ነው።
በመጨረሻም
በኢትዮዽያ ፓርቲዎች የሚመሰረቱ በርእዮተ ዓለም ልዩነት ምክንያት ኣይደለም ካልን ታድያ የጋራ ነጥባቸው ምንድነው? በኢህኣዴግ ሙስና መሰረት ያደረጉ ጥቅማጥቅሞች ያገናኛቸዋል። የተቃዋሚ ፓርቲዎች ኣንድ የሚያደርጋቸው ነጥብ ደግሞ ገ ዢውን ፓርቲ መጥላታቸው ነው።
የመጨረሻ መጨረሻ
በመርህ የሚንቀሳቀሱ ፖለቲከኞች የሉም ማለት ግን ኣይደለም። ይኖራሉ ግን የህዝብ ተቀባይነት በቀላሉ ለማግኘት ይቸገራሉ። ስለዚ ኣናያቸውም።
የኢትዮዽያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሆይ፡ እባካቹ ኣንድ ጠንካራ ድርጅት ፍጠሩ። 33፣65 እየተባላቹ ኣታሳፍሩን።
It is so!!!     Abraha Desta from Mekele 

TPLF’s Hidden Support to Al-Shabab Exposed


By Orion Asmelash
Truth by nature is self-sustained, it does not get old as time goes, nor does it get defeated by the majority, as evil and deceptions get stronger, truth shines more splendidly in the middle of a great confusion and lies. With all that propaganda regarding Al-shabab since 2006, who would imagine what was hidden underneathTPLF’s closets concerning the mysterious dirty affairs it has with Al-shabab?, and who would think that TPLF would work both with Al-shabab and the so called TFGand other ethnic Somalia groups to keep the fire burning?, Well, It is only through time and crisis that truth became more clearer. The international community has been misled big time when it comes to Ethiopia’s doctrine on Somalia. Ethiopia’s Claim of fight against Al-shabab and terrorism is a big lie and deception. Ethiopia neither want Al-shabab to take over Somalia and nor does it want Al-shabab to desist or die. TPLF cannot survive without terrorism. It is through this that the regime got support from the west and stayed in power for 20 years. The people in the horn of Africa knows TPLF from head to foot, they are familiar with its tactics and games. Anyone who observed TPLF’s behavior for the last 20 years will hardly miss what is behind the scene. TPLF leaders and their followers are like a chameleon, they change colors every season but their aim and real character is always the same. Their mind produces nothing good than fertilizing evil thoughts of bigotry and dirty plots. What TPLF says and does is always the contrary. When they say it is good, it means evil; when they tell you it is dark, it means light; when they say it is bitter, it is sweet. When they call for peace, it means for war; when they advocate for justice, it means they have made crimes; when they denounce terrorism, it means they want it. It is always the opposite. They have a very long and extrudable tongue to deceive and mislead others, but for those who know them very well, deep inside their thoughts “they hatch the eggs of vipers and spin a spider’s web”.
TPLF’s music of “Al-shabab” has become like a national anthem. Is TPLF fighting Al-Shabab or supportingETHIOPIA: TPLF’s Hidden Support to Al-Shabab Exposed it? Well, for those who know TPLF’s character it is not hard to scramble their words and speeches. The people in the region have seen the egg long ago before it got hutched. Today, even little children know how to solve TPLF’s cross words. Unless the international community and specially United States are intentionally cooperating or bypassing TPLF’s hidden agenda, it is not difficult to understand the regime’s strategy in Somalia and the region in general. Considering TPLF’s behavior and past track records, including its terrorism activities, such as abducting aid workers, kidnapping foreigners and robbing up banks while they were rebel fighters against the Mengistu Regime before 1991, it is therefore logical to suspect and enquire to see if there is any reason why TPLF would like the spirit of terrorism to continue exist and live in the region. This is not speculation or conspiracy theory; I am not the first to claim this either. I will let the facts speak for themselves. In 2008, South African Ambassador to the United Nations, Dumisani Kumalo, who was basically the chairman of the U.N. Security Council’s Somalia sanctions committee at that time, in his remarks to the Security Council’s said:
“Eighty percent of ammunition available at the Somali arms markets was supplied by TFG and Ethiopian troops,”
No one denies the fact that TFG is controlled and directed by TPLF, thus technically according to Kumalo’s report, 80% of the arms supplied to Al-shabab came from TPLF. Therefore, we should not be surprised when Ethiopia is supporting Al-shabab. The only thing we need to do is to find the reason why Ethiopia supports Al-shabab and other ethnic rebel groups in Somalia? Then, the answer becomes clearer. First, we need to understand TPLF’s method of operation. TPLF is like a wolf in sheep clothing. With its chameleon like long tongue always present itself to the west as an anti-terrorist regime. The United States and the international communities believed it. Not knowing TPLF’s tactical game behind the scene, with TPLF’s lead they all dipped their hands into the bowl of blood shed that they now regret. Eritrea’s continuous advocacy for an all-inclusive political solution for Somalia was refuted, and instead Eritrea was considered as a “spoiler”. Today, after a lot of try and error experiment, the international community realized that Ethiopia’s ill-advised strategy has created the worst humanitarian crisis in history, now it seems that the international community is prepared to change strategy so as to devise something functional to solve the Somalia issue. There is a saying that, “A man who carries a cat by the tail learns something he can learn in no other way”. Those who were stubborn to listen Eritrea’s advice for many years, now seems to embrace Eritrea’s strategic solution, which is an all-inclusive political participation of all parties for a peaceful and lasting solution for Somalia. By now, all parties have understood that every road to Somalia through TPLF is a crooked road and those who follow and walk along TPLF regime will see only crisis and destruction.
Because the international community has started to change strategy on Somalia, Eritrea went a step further by reactivating its IGAD membership to facilitate and pave the right way for Somalia’s political solution. TPLF’s strategy on Somalia seems like it is fading away and Eritrea’s innocent and genuine proposal solution for Somalia is gaining momentum and will soon take over the platform to lead the IGAD member states and the international community to a viable and lasting solution for Somalia’s crisis. TPLF is showing frustration as Eritrea joins IGAD because Eritrea’s strategic solution will bring all Somali parties into one table for a common benefit towards reconstituting Somalia. Ethiopia’s old and failed self-centered tactic of getting aid in the name of managing the Somalia crisis is vividly exposed that it is only intended to prolong TPLF’s life in power and today it is slowly loosing its popularity. TPLF’s paranoia is exposed with its silly and childish behavior at the IGAD council of ministers meeting in Addis Ababa on August 24th. TPLF’s security agents has abused, harassed and threatened Eritrea’s envoy and forcefully expelled Eritrea’s representative Biniam Berhe from the meeting. TPLF’s shameful frustration is a sign of weakness and defeat.
So, why is TPLF choosing instability and crisis as a means of survival to prolong its life expectancy in power? Let’s dig in to it more….
TPLF’s agenda in Somalia and its act of invasion in 2006 was not to fight terrorism but to disintegrate and weaken Somalia. Despite the clear evidence, Eritrea was instead used as a scape goat to conceal Ethiopia’s Evil adventurism. I wonder how many people know that Eritrea, even before it became a nation had been fighting against Bin laden and terrorism since 1989, this is even before the world knows Bin laden, but today, instead of acknowledging Eritrea’s contribution to world peace and security, the country was betrayed by the Security Council repeatedly and unfairly. In the world we live in today, reasonableness, fairness, impartiality and Justice has been continuously trodden underfoot, in its place arrogance and selfishness rules over righteousness. Like in the old times, “The innocent is convicted and Barabas the criminal was released” What a Justice!
Kumalo’s assertion of Ethiopia’s support to Al-shabab needs to be reconsidered. The regime in Ethiopia has managed to stay in power because of Al-Shabab. United States supported and protected TPLF both financially and politically, as a result, TPLF was saved from falling, thanks to its friend Al-shabab. The west has been misled, TPLF is not against Al-shabab, instead mysteriously encourages Al-shabab to remain functional .The Regime’s strategy on Somalia is a no peace and no war situation. To sustain this condition, Al-shabab is a concealed co-partner of TPLF. It is a well-known doctrine of TPLF that as long as Somalia is disintegrated and weakened, the regime’s life expectancy can be prolonged. That is why Ethiopia supplies arms both to the so called TFG and to Al-shabab mysteriously to keep the fire burning. In TPLF’s thinking, a stable Somalia is a threat to its survival. Here, we need some analysis and we should ask why it would cause a threat? Why is TPLF allergic to peace and stability? Well, in their reasoning, since they are a minority group, the only way to continue ruling is when there is disintegration and defragmentation in the region, on one hand easy for them to rule and on the other they get financial and political support in the name of fighting terrorism and managing the crisis.
The minority TPLF group represents 6% of Ethiopia’s 80 million population but controls close to 95% of the social, political and economic affairs of the country. What is more ironic however is, according to one reliable source, “93.5% of all key military positions in the Ethiopian National Defense Forces are occupied by ethnic Tigreans, far in excess of their 6% representation among the Ethiopian population”. So, what does this mean?. A united and integrated Somalia frightens TPLF, a united and strong Eritrea frustrates TPLF, and a united and cohesive Ethiopia terrorizes TPLF. This minority Regime is threatened by any sort of peace and stability. That is why it waged war with Eritrea and Somalia, because it feels uncomfortable to live in a stable and peaceful environment, that is why it chose the divide and rule policy by disuniting the people of Ethiopia in to different ethnic groups. Today, TPLF supports Al-Shabab because defragmented Somalia suites its way of thinking and governance. Therefore, as long as there is Al-shabab, TPLF can stay in power and extend its life expectancy.
This minority regime survives only when there is crisis and fragmentation in the region. Somalia’s disintegration benefits only TPLF. The United States and international community have been deceived and should reexamine TPLF agenda in Somalia. As long as this evil wolf is supported and allowed to continue its destabilizing mission in Somalia, there will be no peace in the Region.

Mar 17, 2013

ፊን ፊሸር የተባለ የስለላ የኮምፕዩተር ፕሮግራምኢትዮጵያ ዉስጥም በሠፊዉ ሥራ ላይ እየዋለ መሆኑን ጥናቱ ይፋ አድርጓል


ፊን ፊሸር የተባለ የስለላ የኮምፕዩተር ፕሮግራም በዓለም 25 ሀገሮች ዉስጥ መሠራጨቱንና መንግስታቱም የገዛ ዜጎቻቸዉን ለመሠለል እንደሚጠቀሙበት አንድ ጥናት አመለከተ። ኢትዮጵያ ዉስጥም በሠፊዉ ሥራ ላይ እየዋለ መሆኑን ጥናቱ ይፋ አድርጓል።
የኢንተርኔት ቫይረሱ ኮምፕዩተር ዉስጥ ከገባ ግለሰቦች በኮምፕዩተራቸዉ ላይ የሚያደርጉትን የፅሁፍ የድምፅና የምስል የመልዕክት ልዉዉጦች ወደዋና መረጃ ማሰባሰቢያዉ ማዕከል ይልካል። ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች RSF ኢትዮጵያ ዉስጥ ኢንተርኔት ላይ የሚደረገዉን ቁጥጥር አስመልክቶ የተጠቀሰዉ የስለላ የኮምፕዩተር ፕሮግራም ሥራ ላይ መዋሉን ጥናቱን ጠቅሶ ለዶቼ ቬለ መግለፁን ዘግበናል። ዶቼቬለ ስለጉዳዩ የጠየቃቸው የኢትዮ ቴሌኮም የኮምንኬሽን ኦፊሰር አቶ አብዱራሂም አህመድ ኢትዮ ቴሌኮም በተጠቀሰው ፕሮግራም እንደማይገለገል በስልክ ተናግረዋል። አቶ አብዱራሂም ስለጥናቱ ውጤት እንደማያውቁ ገልፀው ሆኖም ፊን ፊሸር የተባለው የስለላ የኮምፕዩተር ፕሮግራም ኢትዮጵያ ውስጥ ሥራ ላይ ውሏል መባሉን ከዕውነት የራቀ ሲሉ አጣጥለውታል።
ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት RSF በያዝነዉ ሳምንትባወጣዉ የኢንተርኔት ቁጥጥርን የሚመለከት ዘገባ አምስት ሀገሮችን የኢንተርኔት ጠላት ሲል ፈርጇል። የሶርያ፤ ቻይና፤ ኢራን፤ ባህሬን እንዲሁም የቬትናም መንግስታት የኢንተርኔት መረጃዎችን ለመቆጣጠር ከሚሰነዝሩት የድረገፅ ጥቃት በተጨማሪ ዜጎችን ለመሰለል የግለሰቦችን የኢሜል መረጃ የሚያጠምዱ ፕሮግራሞችን በመጠቀም ግንባር ቀደም ተብለዋል። ከበርካታ ሀገሮች እነዚህ አምስቱ የተመረጡትም ለኢንተርኔት ቁጥጥሩ የሚጠቀሙበት ቴክኒዎሊጂ መራቀቅና በዚህ ስለላ መሠረትም ጋዜጠኞችና ዜጎቻቸዉን በማሰራቸዉ እንደሆነ የRSF የዘመናዊ መገናኛ ብዙሃን ዘርፍ ተመራማሪ ግሬግዋ ፑዤ ገልፀዋል። በተለይም ቻይና የኤሌክትሮኒክ መከላከያዋ ከዓለም ምናልባትም የረቀቀ ተብሎ ሲገመት ይህንኑ ቁጥጥሯን ለማጠናከር የግል ኢንተርኔት ኩባንያዎች ዜጎቿን ለመሰለል የሚረዱ ስልቶችን እንዲያቀርቡላት ማድረጓም ተገልጿል። ኢራን በበኩሏ የራሷን «ሃላል ኢንተርኔት» በሚል አቋቁማ የኢንተርኔት መረጃ ቁጥጥሯን አጠናክራለች። RSF የተራቀቀ ቴክኒዎሎጂን ሳይኖራቸዉ አምባገነን መንግስታት ዜጎቻቸዉን ለመሰለል እንደማይችሉ በማመልከት ለመጀመሪያ ጊዜ ተባባሪ የኢንተርኔት ጠላቶች ሲል የመሰለያ ፕሮግራሞችን የሚሰሩና ለሀገራቱ የሚያቀርቡ ድርጅቶችንም ስም አጋልጧል። ፈላጭ ቆራጭ መንግስታት ዜጎቻቸዉን በኢንተርኔት መረጃ ልዉዉጥ ሳይቀር እንዲቆጣጠሩና እንዲሰልሉ ስልቱን እያስተካከሉ የሚያቀርቡትን አምስት የግል ኩባንያዎችም የዘመኑ «ቅጥረኛ ነፍሰ ገዳዮች» ሲል RSF ወቅሷል።
ኢትዮጵያ ዉስጥ በርከት ያሉ ድረ ገፆች መነበብ እንደማይችሉ ተደጋግሞ የተገለፀ ጉዳይ ነዉ፤ መንግስት በበኩሉ ወቀሳዉን ቢያስተባብልም። የጥናቱ ተባባሪ ፀሐፊ ግሬግዋ ፑዤ ከአምስቱ ሀገሮች ተርታ በዘገባዉ ኢትዮጵያ ያልተጠቀሰችዉ የኢንተርኔት አገልግሎቱ እንደአምስቱ ሀገሮች የተስፋፋ ባለመሆኑ እንደሆነ ለዶቼ ቬለ ገልፀዋል። ያ ማለት ግን ድርጅታቸዉ ክትትል አላደረገም ማለት አይደለም፤
«ባለፈዉ ዓመት ኢትዮጵያ ዉስጥ ምን እንደተደረገ እየተካተልን ቆይተናል። ማለትም TOR የተሰኘዉ ስልት ተዘግቷል፤ የሰዎች ኢሜይል ልዉዉጥ እየሰበረ የሚበረብረዉ DPI የተሰኘዉ ፕሮግራምም ስራ ላይ መዋሉን እናዉቃለን፤ ዛሬ ደግሞ ሲቲዝን ላብ የተሰኘዉ ተቋም ከቶሮንቶ አንድ ዘገባ አዉጥቷል፤ ያም ኢትዮጵያ ዉስጥም አንድ የግለሰቦችን የኮምፕዩተር መረጃ የሚያጠምድ ፕሮግራም መጠቀም መጀመሩን ይገልፃል። ተቋሙ ዛሬ ይፋ ባደረገዉ ዘገባ ፕሮግራሙ ኢትዮጵያ ዉስጥ ኢንተርኔት ላይ የሚካሄደዉን ቁጥጥር የሚያረጋግጥ መረጃ አካቷል።»
ግሬግዋ ፑዤ የጠቀሱት ሲቲዝን ላብ የተሰኘዉ ተቋም ይፋ ያደረገዉ ዘገባ የግለሰቦችን መረጃ የሚያጠምደዉ የኢንተርኔት ፕሮግራም ፊን ፊሸርስ እንደሚባል ይገልፃል። እንደዘገባዉም ኢትዮጵያ በተለይም ከተቃዉሞ ፖለቲካ ቡድኖች ጋ ግንኙነት ያላቸዉ ግለሰቦችን ለመከታተል ትጠቀምበታለች።
ኩባንያዉ ይህን የግለሰቦችን የኢንተርኔት መረጃ የሚያጠምድ ፕሮግራም ለኢትዮጵያ ያዘጋጀዉ የግንቦት ሰባት አባላትን ፎቶዎች በመጠቀም እንደሆነም ዘገባዉ በመዘርዘር ምስሎቹን ያሳያል። ግሬግዋ ፑዤ፤
«ባለፈዉ የበጋ ወቅት ሲቲዚን ላብ ፊን ፊሸር የተሰኘዉ ፕሮግራም ኢትዮጵያ ዉስጥ ሥራ ላይ መዋሉን ደረሰበት። የግንቦት ሰባትን «ስሙን በትክክል ብየዉ እንደሁ አላዉቅም» ምስል የያዘዉ ይህ ህገወጥ ፕሮግራም በርካታ የተቃዉሞ ፓርቲ አባላት በኢሜል አድራሻቸዉ እንዲደርሳቸዉ ተደረገ። እናም ይህ ምስል ትክክለኛ መልዕክት የያዘ ሳይሆን ያ መረጃ የሚያጠምደዉ ፕሮግራም ነዉ። ይህን ፕሮግራም አንዴ ኮምፕዩተርሽ ዉስጥ ከገባ ወደማዘዣዉ ኮምፕዩተር መረጃዎችን በሙሉ እየቀዳ ይልካል። ይህ ነገር ኮፕዩተርሽ ዉስጥ ካለ እያንዳንዷ የምትፅፊያት ነገር ፕሮግራሙን ወደላከዉ አካል ይሸጋገራል።» እሳቸዉ እንደሚሉትም ሲቲዚን ላብ ባደረገዉ ክትትል የግለሰቦችን መረጃ እየቀዳ የሚልከዉ ህገወጥ ፕሮግራም ትዕዛዝ አስተላላፊ የኮምፕዩተር መረጃ ማከማቻ የሚገኘዉ እዚያዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ መሆኑን ደርሶበታል። ኢትዮጵያ ዉስጥ በኢንተርኔት ላይ የሚከናወነዉን ጥብቅ ቁጥጥር እና ስለላ አስመልክቶችም ሲቲዚን ላብ ይፋ ያደረገዉን አዲስ መረጃ በማካተት ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ዘገባ ይፋ እንደሚያደርግም ከወዲሁ ጠቁመዋል።
አበበ ፈለቀ
ሸዋዬ ለገሠ
ሂሩት መለሰ