Apr 23, 2013

በአማራ ክልል ውስጥ ያለው ኦሮሞ ዞን ከተፈጠረለት ለምን የራያና አዘቦ ዞን በትግራይ ውስጥ አልተፈጠረም


ቡልቻ ደመቅሣ 22 /04/2013
የኦሮሞ የፖለቲካ ጉዳይ በየዘመኑ አንድ እርምጃ ወደፊት ሁለት እርምጃ ወደኋላ ሲመሏ ለዘመናት ቆይቷል፡፡ ይህ የሆነው ከአፄ ሚኒሊክ ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡ ከዚያ በፊት፣ የኢትዮጵያ ነገስታት ኦሮሞን ለማሸነፍ ስላልቻሉ በየጊዜው እየተጋጩ እንደምንም አብረው ይኖሩ ነበር፡፡ ፋዘር አልሜዳ የሚባለው የፖርቱጋል ቄስ በዚህ ጉዳይ በሰፊው ጽፏል፡፡ ነገር ግን አብሮነታቸው እንደ ገዥና ተገዥ አልነበረም፡፡ ከአጼ ልብነድንግል ጀምረው እስከ ንጉስ ሳህለ ስላሤ የነበሩት አፄዎች ሁሉ ኦሮሞን ለማሸነፍ እና ለመግዛት ያላደሩጉት ጥረት አልነበረም፡፡
ኦሮሞንና ሀገሩን አሸንፈው ለማስገበር የቻሉት አፄ ሚኒሊክ ብቻ ነበሩ፡፡ እሳቸውም ኦሮሞን ለማሸነፍ የቻሉት ከኦሮሞዎች ቀደም ብለው ከፈረንጆች የጦር መሳሪያ ስላገኙ ነበር፡፡ መሣሪያ ያገኙበትም ምክንያት ከእሳቸው ቀድሞ የነበሩት አንዳንድ አፄዎች ለአውሮፓ መንግስታት “ኢትዮጵያ ብቻዋን ክርስቲያን ሆና በአፍሪካ ውስጥ የምትኖር ሀገር ነች” ብለው የአውሮፓውያን መንግሥታትን ስለለመኑና ስላስረዱ የጦር መሣሪያ ማግኘት ቻሉ፡፡ በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አፄ ሚኒሊክ ሸዋን በሙሉ ለመቆጣጠር ሲነቃነቁ ደብረብርሃን አጠገብ በምትገኘው አብደላ በምትባል መንደር ውስጥ ከጎበና ዳጬ ጋር ተገናኙ፡፡ ጎበና ዳጬም በዚያን ጊዜ በኦሮሞ ገዳ ሥርዓት የሉባና የነበዙ አባ ደክር ወዳጅ የነበሩ፡፡ ከአፄ ሚኒሊክ ለጎበና ዳጬ አንድ ነገር ተናገሩ፡፡ “ወደታች ወደደቡብ እንሂድ፡፡ ወደአቢቹ፣ ገላን፣ ጉለሌ፣ አርሲ አብረን እንዝመት፡፡ አንተ የጋላ ንጉስ ትሆናለህ፣ እኔ የኢትዮጵያ ንጉስ እሆናለሁ ተከተለኝ” አሏቸው፡፡ እንደተባባሉትም ወደታች ወደደቡብ መጥተው የኦሮሞን ጎሣዎች መውጋት ጀምሩ፡፡ ጎበናም ራስ ተባሉ፡፡ ነገር ግን አፄ ሚኒሊክ ለጎበና የገቡትን ቃል ሳይጠብቁ ቀሩ፡፡ ጎበናም ብዙ ጊዜ ከተዋጉ በኋላ እየተዳከሙ ሄዱ፡፡ ነገር ግን የሸዋን፣ የወለጋን (በሰላም የገቡ) እና የከፋን (ከፋም በሰላም ገባ) ኦሮሞዎች ካሸነፉ በኋላ አፄ ሚኒሊክ እራሳቸው ጦርነቱን መምራት ጀመሩ፡፡ ራስ ጎበና በቀየሱት መንገድ ሄደው ሌሎች ያልተያዙትን ሀገሮች ያዙ፡፡ ለምሳሌ ሀረርን፣ ውጋዴንን፣ ሱማሌን፣ ቦረናን ያቀኑት ከዚያ በኋላ ነው፡፡ (እኔ አቀኑ እላለሁ አንዳንድ ሰዎች ግን “ኮሎናይዝ” አደረጉ ነው የሚሉት፡፡ እውነቱን ለታሪክ ተንታኞች እንተዋለን፡፡) ይህ ታሪክ አፈታሪክ ነው፡፡ የታሪክ ምሁራን እንደሚሉት አፈታሪክ የተፃፈ ታሪክ ያህል ዋጋ አለው፡፡ አሁን ልክ አይደለም ብሎ መከራከር ዋጋ ቢስ ይሆናል፡፡ ምክንያቱም ኦሮሞዎች ሁሉ ይህን ያምናሉ፡፡ ያም ሆነ ይህ የታሪኩን እርግጠኛነት የሚያረጋግጠው የራስ ጎበና ሕመም ነው፡፡ (በብስጭት እንደሆነ በእርግጠኝነት የሚናገሩ የእሳቸው ተወላጆች አሉ፡፡)
እኔ እንደብዙ ወገኖቼ ጎበናን አላብጠለጥልም ሰው ስራ መስራት አለበት፡፡ ቤተሰቡን የሚደግፈው የሰራ እንደሆነ ነው፡፡ አለስራ መኖር አይቻልም፡፡ ስለዚህ ራስ ጎበና ስራ አግኝተው ቢሰሩም የፈለጉት ሳይሆን ቀርቶ ታመው ሞቱ፡፡ ይሄ ማንኛቸውም መሪ የሚያረገው ነገር ነው፡፡ አንዳንዱ አላደርግም ብሎ ይሞታል፡፡ ግን ብዙ ሰው ሞትን አይመርጥም፡፡ አፄ ሚኒሊክ ጎበናንም ባያገኙ ማሸነፋቸው አይቀሬ ነበር፡፡ ምክንያቱም በዚህ ጊዜ ከአውሮፓውያን ብዙ የጦር መሣሪያ አግኝተዋል፡፡
ራስ ጎበና ከሚኒሊክ ጋር ያደረጉት ስምምነት ለጊዜው ለኦሮሞ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚሄድ መስሎ ነበር፡፡ ከዚያም በኋላ አፄ ሚኒሊክ ኦሮሞን የገዙበት የባሪያ አገዛዝ ሁለት እርምጃ ወደኋላ እንዲሄዱ አደረጋቸው፡፡ ኦሮሞ ደርግ ላይ ምንም ተስፋ ስላልነበረው የጀነራል ተፈሪ ባንቴ ፕሬዝዳንት መሆን ምንም አልመሰለውም፡፡ ዶክተር ነጋሶ ፕሬዝዳንት ሲሆኑ ለኦሮሞ የተሻለ መስሎ አልታየውም፡፡ ዶክተር ነጋሶም እራሳቸው በስርዓቱ ባለማመን ረግጠው ወጡ፡፡
ከዚያ በኋላ የአፄ ሚኒሊክን የጦር ኃይል መመከት ያልቻለው ኦሮሞ፣ ገባርነትን ለመቀበል ተገደደ፡፡ ሆኖም ግን አፄ ሚኒሊክ ከዚያ በፊት ኦሮሞ ይዞት የነበረውን መሬት ማስለቀቅ ስላልቻሉ ኦሮሞ በአፄ ልብነድንግል ጊዜ በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ይዞት የነበረውን መሬት እንደያዘ ቀረ፡፡ እዚህ ላይ እናስታውስ፡፡ የወሎ አሮሞና ትግራይ ውስጥ ያሉት ራያና አዘቦ ኦሮምኛ ቋንቋቸውን እየረሱ አማርኛ ወይም ትግሪኛ መናገር ጀምረዋል፡፡ በአማራ ክልል ውስጥ ያለው ኦሮሞ ዞን ከተፈጠረለት ለምን የራያና አዘቦ ዞን በትግራይ ውስጥ አልተፈጠረም፡፡ ይኼ የሚያሳየው ሕገ መንግስቱ በተፃፈበት ጊዜ (በ1986 ዓ.ም) ህወሓት የነበረውን ፍጹም የበላይነት ነው፡፡
ዛሬ የኦሮሞ ሕዝብ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ቢያንስ 35 በመቶ መሆኑን ሁላችንም እናውቃለን፡፡ ሕዝቡም ወደ ሰላሳ ስድስት ሚሊዮን ይገመታል፡፡ የኦሮሞ መሬት ስፋቱ 387,000 ኪሎ ሜትር ይሆናል፡፡ ማለትም ጀርመንን ያክላል ማለት ነው፡፡
Read more at  http://www.fetehe.com

Apr 22, 2013

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት በፖሊስ ተከቦ ስብሰባውን አከናወነ


የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት ዋና ጸሀፊ አቶ ትግስቱ አወሉ በተለይ ለፍኖተ ነፃነት እንደተናገሩት የፓርቲው ብሔራዊ ምክር ቤት በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡

UDJበፓርቲው ስትራቴጂክ እቅድ መሰረትየአንድነት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ በመጪው አመት መስከረም ወር የመጨረሻ ሳምንት ላይ እንደሚያካሂድ አስረድተዋል፡፡ በፓርቲው ደንብ ለሊቀመንበሩ በተሰጠው ስልጣን መሰረት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ የነበሩትን ኢ/ር ዘለቀ ረዲን በስራ አፈፃፀም ብቃት ማነስ ምክንያት አንስተው በቦታው አቶ ስዩም መንገሻን መተካታቸውን ለምክር ቤቱ አሳውቀዋል፡፡ ምክር ቤቱም ሹመቱን አፅድቋል፡፡
አቶ ትግስቱ ጨምረውም ባለፈው ረቡዕ በሰንደቅ ጋዜጣ ለአንድነት ፓርቲ አሉታዊ አመለካካት ባለቸው አካላት የወጣውን መሰረተ ቢስ ውንጀላና በፓርቲው ስራ አስፈፃሚ አባል በነበሩት ኢንጅነር ዘለቀ ረዲ በተሰጠው የሀሰት መረጃ ዙሪያ ኢንጅነር ዘለቀ በተገኙበትና ሀሳባቸውን በነፃነት በገለፁበት ሁኔታ ሰፊውይይት መደረጉን አብራርተዋል፡፡
ምክር ቤቱ በሰጠው ውሳኔ መሰረትም ነገ ሰኞ ሰንደቅ ጋዜጣ ያወጣውን ሀሰተኛ መረጃ የሚያስተካክል መግለጫ እንዲሰጥ ኢ/ር ዘለቀን በሚመለከትም ጉዳዩ ለብሔራዊ ዲሲፕሊን ኮሚቴ እንዲመራ መወሰኑን የምክር ቤቱ ጸሀፊ ገልፀዋል፡፡ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት ቅዳሜ ሚያዝያ 12 ቀን 2005 ዓ.ም ስብሰባ ባደረገበት ወቅት ከአስር የበለጡ የፌደራል እና የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት በፓርቲው ዋና ጽ/ቤት ዙሪያ ከበባና ቅኝት ሲያደርጉ እንደነበር የፍኖተ ነፃነት ጋዜጠኞች ዘግበዋል፡፡
ፍኖተ ነፃነት

Apr 13, 2013

An int’l lawyer says the forced eviction of Amhara is “an ethnic cleansing”


     
April 3, 2013

Dr. Yacob Hailemariam, a former UN prosecutor in the Rwanda genocide trial in Tanzania, said to ESAT that the current forced eviction of Ethiopians of the Amahra ethnic origin from Benishangul Region and also last year from Gurafarda, South Ethiopia, is “an ethnic cleansing crime”.
Dr. Yacob said though the crime is not “genocide”, it is an “ethnic cleansing” which could be instigated anytime and is punishable according to Ethiopian or international laws. The scholar advised Ethiopian officials to think about the issue twice.
“If Ethiopians inside and outside the Country present tangible evidences to the United Nations Security Council, the perpetrators of this act could be accused” Yacob added. The acts could destabilize the Region’s stability, He said.
Recalling the statements of the late Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi, who once stated that the evictions of Amharas was not because of their ethnicity but because they cleared forests and illegally settled, Yacob said “even if they cleared the forests, they should be accused for deforestation but not be deported back to their native regions”.
Asking every Ethiopian to denounce this act, the Scholar also said that all Ethiopian officials are responsible for this crime and the arguments being presented by the Government are “completely unacceptable”.

Woyane ruling Ethiopia is pushing every button of Ethiopians



The notorious and corrupt ethnic Apartheid regime of Woyane ruling Ethiopia is pushing every button of Ethiopians. If any Ethiopian has iota of doubt that Woyane is anything but a violet, corrupt and stupid regime in cover of Ethnic Federalism and development, they need to get their head checked. The time has come for all Ethiopians with out exception to burry the ethnic Apartheid regime and move on to better alternative sooner than later. Ignorance of that reality or making up off the wall noises to divert the issue isn’t going to be an excuse anymore. It only proves as a desperate attempt to preserve something proven to be rotten or the goodies it provides for those that are willing to stoop at its level.
‘Stupid is as stupid does’ is an expression that demonstrates the action of one’s stupidity. It also extends to one’sThe notorious and corrupt ethnic Apartheid regime Ethiopia. imagination in thinking her/his stupidity can outsmart the rest. Such mindset further makes stupidity a virtue for those that live in a bubble of the Apartheid system.
Unlike anytime, Woyane and its entourage of messengers-of-death and corruption are testing the limits of all Ethiopians. Surprisingly, the stooges still couldn’t figure out their stupidity is beyond anything we have seen in modern times; with the exception of a few brutal tyrannies in Africa and the Middle East. Tyranny is its own worst enemy because it congregates stupid people. Then again, tyranny wouldn’t survive without them.
Therefore, it is not unusual for Woyane to assemble violent, corrupt and stupid individuals incapable of rational thinking. It seems, the messengers’ stupidity is getting out of hand and overwhelmed even the top warlord of the ethnic Apartheid regime that unleashes them to terrorize and robe the people with impunity. It appears the warlords are trying to restrain the same messengers of death and corruption they unleashed and used to get Woyane where it is to cause havoc on the population.
The recently reported ethnic cleansing of Amharic speaking Ethiopians from Western and Southern Region and the atrocity inflected on Ethiopians of the Muslim faith are some of the indication the Apartheid regime is running out of option to stay alive. In the name of development and fighting terrorism, Woyane is hoping against hope to cover up its corruption and atrocities to extend its rule one day at a time. It is a tragic reminder of how far Woyane is willing to go to incriminate the people of Tigray it claims to represent just because… it wants to continue its illegitimate rule and corruption in their name.
Few weeks ago, in unprecedented futility to hoodwink the public again, the Woyane ethnic Warlords that pause as Ethiopian People Federal Democratic Republic (EPFDR) completed their latest drama on the party’s ninth general assembly conference.
The circus with the same notorious TPLF’s ethnic warlords and their junior partners dressed up like clowns was an attempt to sell the public the next phase of Woyane’s strategy to lie its way out of its crimes and stay alive. Azeb Mesfin, the widow of the late tyrant Melse Zenawi and known as the queen of corruption was also part of the acting crew defending her late husband and partner in crime that died a destitute man with no bank account in his name, according to her. Was she attempting to make us believe there are some innocent ethnic warlords in the Woyane family or is it a sign some of the warlords going to bit the dust to save face? Regardless, her act was hilarious for those that knew the man as mastermind of Woyane’s corruption, but, for the blind Woyane supporters that are led by a blind man they may see selfless visionary leader to believe her.
When her recital wasn’t enough, the notorious ethnic warlord and President of the so called Tigray Region chastised his junior ethnic warlord; claiming his ‘Region’s development’ is due to good governance of his leadership instead of TPLF’s daylight robbery of the nation in the name of the hostages held in the Region he was appointed to subjugate. Before we know it, the shameless TPLF Warlord is going to say robbing the nation’s resources and collecting donation around the world to damp it in the Tigray Region is the visionary leadership of the late Melse Zenawi’s new Developmental State theory. Let’s face it; the late tyrant was good making his clueless stooges feel good about themselves in believing robbery is development. We must agree he wasn’t an ordinary tyrant we are used to in Africa.
The gathering of the clowns that make and break the law believe they can manufacture a drama and show it on the only television they control and to go on in their business of corruption and atrocity. Sadly to say, it worked before, and the collection of blind stooges and apologists go along with it and pretend they are living a life worth living on the expenses of Ethiopians.
Imagine what the hapless ethnic warlords are telling us. Apparently, they still couldn’t make up their mind who gave them the mandate to rule Ethiopia? They use to say, and still do; Ethiopia is TPLF’s war trophy willing to suck her dry until some one forces them to surrender. Another time, they told us Woyane is an elected government by 99.64% of the popular votes, thus, legitimate regime to rule. When that doesn’t work, they came up with yet another lam excuse; growing the economy by double digit entitles them to rule for eternity. When noting works and desperation set-in; fighting terrorism or bashing their favorite brand enemy, the Amahars comes in handy to justify their criminal rule. When everything is bleak; there are always the ‘extreme Diasporas’ that ‘hate Tigrians’ to cry about.
Fortunately, noting seems to work for the ethnic warlords except terrorizing and robbing Ethiopians in to silence with their death squad. Woyane warlords are like an obsessed man going ballistic for being rejected by a woman he saw and loved insight; terrorizing her to be with him or… else. In politics, that kind obsession to be loved by terror turns in to ugly episode like we see with Woyane’s out of control behavior. Civilized politicians take rejection with a grain of salt and move on to do better next time around, but not Woyane warlords. Instead, they lie to themselves and the public with straight face the entire population loves them and go out terrorizing the people to force love them or… else. It is the ultimate ugliness of uncivilized regime that is willing to kill when rejected by popular demand.
At the meantime, more revelation surfaced to show Woyane’s love for the late Fascist regime than Ethiopian rulers that humiliated it. By jailing patriotic Ethiopian that protested against Fascism that cost us millions of our people’s lives the shameless warlord showed their true color. Not one TPLF warlords came out in protest of Fascism nor Woyane officially or unofficially oppose when Rodolfo Graziani, the butcher of Ethiopia is honored in Italy while warlords goes out of their way to manufacture lies to dishonor legendry Ethiopian leaders and war heroes that buried Fascism for good to inspire the independence movements of the entire Africa and beyond. Nor we have heard anything from Woyane stooges and apologist protesting against honoring the Fascist warlord. The last and only time stooges were protesting was against Egypt for the rights of Ethiopia to use the Nile water in front of the White House in Washington DC. Indecently, the Italian construction company Salini is given an exclusive contract to build the Grand Dam as well as others in partnership with Woyane. Talk about selling the country in a hand basket.
Before we know it, Woyane is going to rewrite history; praising Graziani as a great and visionary leader of Ethiopia that grew the economy by double digit and built roads in the honor of Zenawi Asers, the father of the late tyrant that served Rodolfo Graziani. Better yet, his statue would come in handy on the African Union Headquarter as Woyane gift for Africans. As shameful as it may sound, noting is impossible under Woyane.
This is the newest low for Woyane even its stanch stooges can’t swallow the degenerated behavior of the regime they love to death. Once again, it proved for one and all, Ethiopia has been under the rule of Fascist sympathizers unhappy Ethiopians buried their hero for good.
Can this be the prove needed that would break the back of the collection of Woyane stooges that are hell-bent to defend the ethnic Apartheid and Fascist loving regime tooth and nail? Ethiopians can’t wait to hear from Woyane stooges and apologist that are afraid to come out of their hiding to tell us why their beloved regime flirting with the long buried Fascist regime? Most importantly, why are they associating the people of Tigray with Fascist loving Apartheid regime? More question, no answer.
The good news is Ethiopians from all walks of life are finally coming together to burry the rogue and Fascist sympathizer Woyane regime for good. The sign is on the wall when we see the nervous Woyane stooges running like mad dogs biting every Ethiopian. The Warlords are feeling the pain of the Apartheid system they set up coming to bit them. The apologists; after they buried the ethnic warlord extraordinary with drama full of crocodile tears are wondering what they got themselves in flirting with an ethnic Apartheid regime for this long.
Unlike many, I am a firm believer Woyane from the get go came out to destroy the people of Ethiopia via Tigray by faking to represent them. Already it damaged their image associating them as Ethiopian haters, corruptible, collaborators of treason and atrocities while branding them as lover of the notorious tyrant Melse Zenawi. If that isn’t an insult to the people Ethiopia in general and Tigrians in particular that supposedly elected the notorious TPLF as their sole representative we don’t know what it is.
Woyane cadres that amassed and laundered millions of dollars robbing Ethiopians is good example of how far Woyane will go to incriminate the people of Tigray. If we think about it, no one is public enemy # 1 than the messengers of the Apartheid regime bribed to destroy the people of Tigray’s image against their country. After all, tyrants come in all shapes and forms and go but, their willing massagers-of-death and corruption are the one that execute the crimes as the tool the regime as they did serving Fascist. Therefore, Ethiopians should look no further than the willing Apartheid regime’s cadres that are causing havoc on behalf of TPLF.
Our problem is everybody is struggling for its own as hyphenated ethnic, religious, region…group as the Apartheid Woyane wanted us. Without knowing it we helped Woyane to institute the Apartheid system that is foreign to Ethiopians just like Fascist Italy attempted and failed. Like father like son the late Melse Zenawi happened to be the mastermind of the whole Apartheid system. Talk about visionary leader, it is more the blind leading the blind.
The few exceptions that fight for united and democratic Ethiopia are smeared as the old establishment by none other than Woyane just like Fascist Italy did. Any one party or group that divide Ethiopians by religion, ethnicity, region is doing the Woyane bidding to undermine the people from coming together to end the Apartheid regime sooner; as our people did with the Fascist regime then.
The struggle of Ethiopians of Muslim faith is an example of Ethiopiawinet at its best and at its worst. At best, because Ethiopiawinet is in the blood of every Ethiopian; contrary to what the Apartheid regime of Woyane and rogue groups wanted us to believe. In our history no one group tolerated when any of our people assaulted by a rogue regime or anyone else, especially foreigners. For that, Woyane with questionable identity will pay dearly in the coming years. Likewise, contrary to what the rogue Woyane regime want us to believe Ethiopians of the Muslim faith practice true Islam and their love for country remains the center of their religion as proven again and again to the envy of the world. In fact, Ethiopians must teach the essence of Islam for the rest of the world than the other way around; as Woyane and its Godless massagers are attempting to do through their Godless cadres. Therefore, Ethiopians at best as Ethiopians regardless of where, when how.
At worst, unlike our tradition and history Ethiopians struggle should never be separately. We failed to close rank when it comes protecting our country and people first and open the door for the rogue regime and the like to break us apart to the point of asking permission to practice our Ethiopian religions and to celebrate our Ethiopiawinet. This blunder cost us a lot and contributed to institute the Apartheid system Woyane set up so that we see each other as enemy; segregated according to TPLF design. Our collective struggle to remain independent people was reduced by a rogue group that claims to represent the people of Tigray, a black eye in our history and on the people of Tigray. As the Ethiopian Imam from Canada put it ‘there is no religion without our country’.
The truth is Ethiopians must never ask the illegitimate Apartheid regime or anyone else to give us something that doesn’t belong to them. Our collective demand must be one and only one; surrender to the people’s will. Peaceful or violent, Woyane must and will surrender to the people will. So far our division; pandering to ethnic peddlers, political prostitutes and economic scavengers left our people venerable for Woyane and the like to run over us.
To achieve victory, the only thing we need to do is come together as proud Ethiopians once again and demand surrender for democratic rule. Whoever is on the way from bringing us together is the enemy of our people.
The self declared minority Apartheid regime and its scavengers’ worst fear is Ethiopians coming together. Therefore, making dramas to divide by instigating ethnic, religious and economic conflicts and diversion are the tool in its arsenal. Everything it did and does since its inception is against Ethiopians from coming together. Therefore, we will be fools to take Woyane’s led when it breaks us apart with propaganda, bribes and favor to use us as Weapon of Mass Distraction on our people. When we remain silent or celebrate the suffering of our people just because… they are not from our ethnic group and religion or region we are no better than Woyane itself.
Let us not drag our feet to extend the misery of our people under an Apartheid system that already caused so much pain and suffering to our people. We must come together to make anyone that harm our people and country pay the ultimate price for treachery.
Ethiopians will win; let the Woyane stooges know there is no choice but to surrender

Apr 11, 2013

‹‹በሕዝብ የተመረጥኩ ነኝ›› ብሎ የሚያምን መንግሥት ‹‹ሕዝብ አለቃዬ ነው›› ብሎ ማመንም አለበት


ሕገ መንግሥታችን ሥልጣን የሚይዝ መንግሥት በሕዝብ ድምፅ ብልጫ የተመረጠ መሆን አለበት ይላል፡፡ እንዲህ ዓይነት ጉድለት አለው እንዲህ መሰል ችግር ነበረው ቢባልም፣ በተግባር ምርጫ የሚካሄድበት አገርና ሕዝብ ሆነናል፡፡
ምርጫ በማካሄድ መንግሥትን ሥልጣን ላይ ማስቀመጥ ማለትና ለገዥው ፓርቲ ሕዝባዊ ድምፅ ሰጥቶ በአመራር ላይ ማስቀመጥ ማለት ግን በመንግሥት ላይ ከፍተኛ ኃላፊነት የማኖር ተግባር ነው፡፡ ኃላፊነቱም ሕዝብን በግዴታም በውዴታም የማገልገል ጉዳይ ነው፡፡ ምክንያቱም ሕዝብ መንግሥትን የሚመርጠው፣ አመራርን የሚመርጠው፣ አስተዳደርን የሚመርጠው ‹‹አገልግለኝ›› ብሎ ነው፡፡
ስለሆነም በሕዝብ ተመርጦ ሥልጣን ላይ የተቀመጥኩ መንግሥት ነኝ የሚል ገዥ ፓርቲ አለቃዬ የመረጠኝ ሕዝብ ነው በማለት ማመን አለበት፡፡ በሕዝብ መመረጥ መብቴ ነው የሚል ገዥ ፓርቲ ሕዝብን ማገልገል ግዴታዬ ነው ብሎም ማመን አለበት፡፡ ሕገ መንግሥታችንም ያስገድደዋል፡፡
ሕዝብ አለቃዬ ነው፣ ሕዝብን ማገልገል ግዴታዬ ነው ብሎ የሚያምን መንግሥት ደግሞ የሕዝብን ጥያቄ ይመልሳል ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ኢሕአዴግ እንደ ገዥ ፓርቲ ራሱን መጠየቅ፣ መፈተሽና መገምገም ያለበት በእውነት የሕዝብን ጥያቄ እየመለስኩ ነው ወይ? ብሎ ነው፡፡
ሕዝብ መልካም አስተዳደር እንዲኖር እየጠየቀ ነው፡፡ ሕዝብ እንደ አለቃ መንግሥትን ሥልጣን ላይ ያስቀመጥኩህ መልካም አስተዳደር እንድታመጣልኝ ነው፡፡ የት አለ መልካም አስተዳደሩ እያለ ነው፡፡
ኢሕአዴግ ደፈር ብሎ አዎን ሕዝብ ሆይ የሚገባኝን መልካም አስተዳደር ስላልሰጠሁህ ይቅርታ እጠይቃለሁ፤ አሁን ግን አሟላለሁ ማለት አለበት፡፡ የት አቤት እንደሚባል እየጠፋ ነው፡፡ መልስ ሰጪ እየታጣ ነው፡፡ እንባ ሲፈስ እንጂ ሲታበስ አይታይም፡፡ መልካም አስተዳደርን እውን አድርግ የሚለውን የሕዝብ ትዕዛዝ መንግሥት እንደታዘዘው እየፈጸመው አይደለም፡፡ መመረጥን እንደ ‹‹መርህ›› የሚወስድ መንግሥት ሕዝብን ማገልገል ግን ‹‹ገጠመኝ›› እያደረገ ነው፡፡
ሕዝብ ከሙስና የፀዳ አገልጋዩን ሠራተኛና ሹም ይፈልጋል፡፡ ሲመርጥም ይህን አገኛለሁ ብሎ ነው፡፡ ከሙስና የፀዳችሁ ሁኑ፣ ከሙስና ፀድታችሁ እኔን አገልግሉ የሚል ትዕዛዝ ነበር ያስተላለፈው፡፡ ለዚህ ትዕዛዝ ግን ‹‹ጥሪ አይቀበልም›› ምላሽ እየተሰጠ ነው፡፡
በሕዝብ ተመርጠው ሹመት ላይ የተቀመጡት ኃላፊዎች ትዕዛዙን ጥሰው ለግላቸው ጥቅማ ጥቅም እየተገዙና እየተረባረቡ ናቸው፡፡ የአገር ሀብት እያባከኑ ናቸው፡፡ ራሳቸውን ከሕዝብ በላይ እያደረጉ ናቸው፡፡ ተገዥነታቸው ለሕዝብና ለሕገ መንግሥት መሆኑ ቀርቶ ለገንዘብ፣ ለንብረትና ለጥቅማ ጥቅም ሆኗል፡፡
ሕዝብ ኑሮ ተወዷል፣ ሸክሙ ከብዶኛል፣ አሻሽሉት የሚል ትዕዛዝ ለመረጣቸው ኃላፊዎችና ላስቀመጠው መንግሥት እያስተላለፈ ነው፡፡ መንግሥት ግን ይህን የአለቃ ትዕዛዝ እያዳመጠና እየመለሰ አይደለም፡፡ መፍትሔ እየሰጠበት አይደለም፡፡
ሕዝብ ኑሮው እንዲሻሻል ባዘዘ ቁጥር መንግሥት ወዲያው ኑሮን ያሻሽላል ማለት አይደለም፡፡ ጊዜ ይፈጃል ሒደት አለው፡፡ ነገር ግን ትኩረት ሰጥቶ ርብርብና እንቅስቃሴ መጀመርና እንዴት እናሳካው ብሎ ከሕዝብ ጋር ሆኖ በፍጥነት መጀመር አለበት፡፡ ይኼ ጥረት አልተጀመረም፡፡ የሕዝብ አለቃነትና የመንግሥት ታዛዥነት በተግባር እየታየ አይደለም፡፡ ሕዝብ የመንግሥት ኃላፊዎች ኮራ፣ ጠንከር ያሉ፣ ብቁና ታታሪ እንዲሆኑ ይፈልጋል፡፡ ያዛል፡፡ ራሳቸው ኮርተው አገርን የሚያኮሩና የአገርን ክብር እንዲያስጠብቁ ይፈልጋል፡፡ ግን ይህንን የሕዝብ ትዕዛዝ መንግሥት በተሟላ መንገድ እያከበረውና እየተገበረው አይደለም፡፡ የሚልፈሰፈሱ፣ ለባለሀብት አሽከርና ተላላኪ የሆኑ፣ አገርንና ሕዝብን ከሚያኮሩ ይልቅ የሚያሸማቅቁና የሚያሳፍሩ ‹‹ክብር አልባ›› ኃላፊዎችም እየተስተዋሉ ናቸው፡፡ በሚያስገርም፣ በሚያሳፍርና በሚያናድድ ሁኔታ፡፡
ሕዝብ መንግሥትን እያዘዘ ያለውና መንግሥትም ሕዝብ አለቃዬ ነው ብሎ ማመን ያለበት፣ ጉዳይ ብዙ መልኮችና ገጽታዎች ስላሉት ነው፡፡ ሕዝብ ስለአገሬ ግልጽ፣ ወቅታዊ፣ ሀቀኛና ሚዛናዊ መረጃና መግለጫ እፈልጋለሁ እያለ ነው፡፡ እያዘዘ ነው፡፡ ነገር ግን በሕገ መንግሥቱና በሕጉ መሠረት ከመጓዝ ይልቅ መንግሥት የራሱን መገናኛ ብዙኀን በማጠናከር ላይ ብቻ ስላተኮረ የሞኖፖሊነት ባህርይ እያሳየ ነው፡፡ የሕዝብ ትዕዛዝ እየተከበረ አይደለም፡፡ የሕዝብን አለቃነት መንግሥት እያመነበት አይደለም፡፡ በሕጉ መሠረት ቴሌቪዥንም ለግሉ ዘርፍ ፈቅዶ፣ የግል ፕሬስንም አጠናክሮ ጎን ለጎን የተለያዩ ሐሳቦች የሚንሸራሸሩበትና የመረጃ ፍሰት የሚጠናከርበት ሁኔታ መፈጠር አለበት፡፡ ታዛዥ ጠፋ እንጂ አለቃው ሕዝብ እያዘዘ ነው፡፡
ያለፈውን ድክመት መንግሥት በሚገባ ፈትሾና መርምሮ ለወደፊቱ ይህ ስህተትና ጉድለት እንዳይደገም ይጠንቀቅ፡፡ ሰሞኑን ምርጫ ይካሄዳል፡፡ ከሁለት ዓመት በኋላም ዋናው ምርጫ አለ፡፡
ለዚህ ምርጫ ኢሕአዴግ ሲዘጋጅና አሁንም በምርጫ አሸንፌ ገዥ ፓርቲና መንግሥታዊ ኃይል ሁኜ እቀጥላለሁ የሚል ከሆነ፣ ደግመን ደጋግመን የሕዝብን ፍላጎትና እምነት እንዲያስታውስ እንወተውታለን፡፡ የሕዝብ ፍላጎትና እምነትም ቀላልና ግልጽ ነው፡፡
‹‹በሕዝብ የተመረጥኩ ነኝ›› ብሎ የሚያምን መንግሥት ‹‹ሕዝብ አለቃዬ ነው›› ብሎም ይመን!!

ህዉሐት በቤንሻንጉል



 የአመራሮቹና የካድሬዎቹ ያልተገባ ውሳኔ 1,346 አባወራዎችን ጨምሮ 3,240 ቤተሰቦቻቸው እንዲፈናቀሉ መደረጉንም አምነዋል

ከቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ካማሽ ዞን ያሶ ወረዳ የተፈናቀሉ የአማራ ክልል ተወላጆች ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉት በበታች አመራሮች ግብታዊ ዕርምጃ በመሆኑ፣ ወደነበሩበት እንዲመለሱ የክልሉ መንግሥት ጥሪ አቀረበ፡፡

የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አህመድ ናስር ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ኪራይ ሰብሳቢ ያሉዋቸው የበታች አመራሮች
 በፈጠሩት ችግር የተፈናቀሉ 1,346 አባወራዎች ወደ ስፍራው እንዲመለሱ ጥሪ ቀርቧል፡፡ 


የተንጣለለ መሬትና የአምስት ብሔረሰቦች ክልል የሆነው ቤኒሻንጉል ክልል፣ በተለይ ከአማራና ከኦሮሚያ ክልል የመጡ በርካታ ሰፋሪዎች ይኖሩበታል፡፡ ከእነዚህ ክልሎች ከመጡ ዜጎች መካከል የእኩል እያረሱ የሚኖሩም በርካቶች ናቸው፡፡ ከዛሬ 28 ዓመት በፊት በክልሉ ውስጥ መኖር የጀመሩ ዜጎችም ተፈናቅለዋል፡፡ እነዚህ በሺዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች ያለመጠለያ ከመቅረታቸውም በላይ ለልመና መዳረጋቸው ሲነገር፣ ዘመድ ያላቸው በየዘመዶቻቸው መጠለላቸው ታውቋል፡፡ በዚህ የማፈናቀል ዘመቻ ለበርካታ ዓመታት የኖሩና መታወቂያ ያላቸው ዜጎች መፈናቀላቸውን ከተፈናቃዮች ለመረዳት ተችሏል፡፡

የክልሉ መንግሥት ባወጣው የመሬት ፖሊሲ መሠረት ሕገወጥ ሰፋሪዎችን በአግባቡ ለማስፈር ዕቅድ የያዘ ቢሆንም፣ ይህ ዕቅዱ ባልተጠበቀ ሁኔታ መመርያ ሳይሰጥበት በበታች የወረዳና የቀበሌ ካድሬዎች ያልተገባ ተግባር የተፈጸመ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡

የአመራሮቹና የካድሬዎቹ ያልተገባ ውሳኔ 1,346 አባወራዎችን ጨምሮ 3,240 ቤተሰቦቻቸው እንዲፈናቀሉ መደረጉንም አምነዋል፡፡ ተፈናቃዮቹ ግን ብዛታችን ከ5,000 ይበልጣል ይላሉ፡፡

ጉዳዩ ያሳሰበው የአማራ ክልል መንግሥት ከቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል መንግሥት ጋር ውይይት ማድረጉን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በውይይቱ ወቅት የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል በተፈጠረው ስህተት ማዘኑን መግለጹን አቶ አህመድም ገልጸዋል፡፡ ዜጎችን በማፈናቀል ስህተት በፈጠሩ አመራሮች ላይ ግምገማ ተካሂዶ ዕርምጃ እንደሚወሰድና ሕገወጥ የሰዎች ፍልሰትን ለማስቀረት የተቀናጀና ዘላቂነት ያለው ሥራ እንደሚሠራ አቶ አህመድ አስረድተዋል፡፡

አቶ አህመድ በክልላቸው በርካታ የአማራ ተወላጆች እንደሚኖሩና ሥልጣን ይዘው የሚገኙ በተለያዩ የአመራር እርከኖች ላይ ያሉ መኖራቸውን አስረድተዋል፡፡ ክልሉ ዜጎችን የማፈናቀል ሐሳብ እንደሌለውና የክልሉን የተፈጥሮ ሀብት ከውድመት ለመከላከል የግድ ሕገወጥ ሠፈራ አደብ መግዛት እንዳለበት ግን አስታውቀዋል፡፡ ይህንንም ለማድረግ ክልሉ ባወጣው የመሬት አጠቃቀም ፖሊሲ መሠረት ተግባራዊ እንደሚደረግ አስታውቀው፣ በሰሞኑ ሕገወጥ ዘመቻ የተፈናቀሉ ዜጎች ግን ተመልሰው ሰላማዊ ሕይወታቸውን መምራት እንደሚችሉ አረጋግጠዋል፡፡

በተያያዘ ዜና የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) እና የሰማያዊ ፓርቲ ከቤኒሻንጉል ጉምዝና ከሌሎችም ክልሎች የአማራ ብሔራ ተወላጆች መፈናቀላቸውን አስመልክቶ ባስተላለፉት የተቃውሞ መግለጫ፣ እስከ አሥር ዓመታትና ከዚያም በላይ ከኖሩበት ቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል የተፈናቀሉ የአማራ ብሔር ተወላጆች፣ በአማራ ክልል በተለያዩ መጠለያ ጣቢያዎች መሆናቸው እጅግ በጣም አሳሳቢ በመሆኑ መንግሥት ሊያስብበት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

ሁለቱም ፓርቲዎች በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቁት፣ ከአንድ ዓመት በፊት ከደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ከጉራፈርዳ ወረዳ በሺሕዎች የሚቆጠሩ የአማራ ብሔር ተወላጆች መፈናቀላቸውን፣ እንዲሁም በቅርቡ ደግሞ በሶማሌ ክልላዊ መንግሥት ከጅጅጋ ከተማ በሺሕዎች የሚቆጠሩ የአማራ ብሔር ተወላጆች ከኖሩበትና ንብረት ካፈሩበት ቀያቸው መፈናቀላቸውን ያስታወሱት ፓርቲዎቹ፣ አሁን መታሰብ ያለበት ነገሮች ወዴት እያመሩ መሆኑንና በቀጣይ ሊፈጠር የሚችለውን ሁኔታ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ዜጎች የሚፈናቀሉበት ምክንያት ፖለቲካዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ወይም ብሔርተኝነት፣ የሚፈናቀሉበትም መንገድ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተቀበለቻቸውንና ስምምነት ያደረገችባቸውን የሰብዓዊ መብት ድንጋጌዎችን ያላከበረ መሆኑን ፓርቲዎቹ ገልጸዋል፡፡ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 14 ስለሰብዓዊ መብቶች የሰፈረውን ድንጋጌና በአንቀጽ 25 የእኩልነት መብትን አስመልክቶ የተቀመጠውን መብት የሚፃረር ድርጊት እየተፈጸመ መሆኑን የገለጹት ፓርቲዎቹ፣ ዜጎች በአስገዳጅ ሁኔታ የተፈናቀሉት በአንድ ሕገ መንግሥትና ሉዓላዊነት አገር ማዕቀፍ ውስጥ መሆኑን፣ መፈናቀላቸውንና ስደታቸውን ተከትሎ እየተከሰተባቸው ያለው ማዋከብና ድብደባ አሳሳቢና አነጋጋሪ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

በደቡብ ክልል በጉራፈርዳ ወረዳ፣ በሶማሌ ክልል በጅጅጋ ከተማ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያሶ ወረዳ የተፈናቀሉ የአማራ ብሔር ተወላጆችና በኦሮሚያ፣ በጋምቤላ፣ በሶማሌና በሌሎችም ክልሎች የተፈናቀሉ ዜጎች ጉዳይ ያስከተለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ ማኅበራዊ ቀውስ፣ በየክልሉ በሚኖሩ ቀሪዎቹ ዜጎች ላይ በሰላም ሠርተው የመኖር ፍላጎትና ሀብት ባፈሩበት ቀዬ የመኖር ጥያቄ ላይ ሥጋት እየፈጠረ መሆኑን መንግሥት ልብ ሊለውና ሊያስብበት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ በመሆኑም መንግሥት በዜጎች ላይ እያደረሰ ያለውን መፈናቀል በአስቸኳይ እንዲያቆም፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት እያካሄደ ያለውን ኢሰብዓዊና ሕገወጥ ተግባር እንዲያቆምና እንዲታቀብ፣ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ለተፈናቃዮቹ ዜጎች ጊዜያዊ መጠለያ፣ አልባሳትና ምግብ እንዲያገኙ እንዲያደርግ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሕዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው ማፈናቀል ሕገ መንግሥቱን የጣሰና ኢትዮጵያን የሚጎዳ ተግባር በመሆኑ፣ ድርጊቱን የፈጸሙ ክልሎችም ሆኑ ግለሰቦች በሕግ እንዲጠየቁ እንዲያደርግ ፓርቲዎቹ ጠይቀዋል፡፡

Apr 9, 2013

የወያኔ ዘረኝነት (Apartheid ) በቂሊንጦ እስር ቤት




እንደሚታወቀው ከህወሐት/ኢህአዴግ ሥርዓት መገለጫ ባህሪያት አንዱና
ዋነኛው ዘረኝነት ነው፡፡ ይህ ዘረኛ ሥርዓት ዓላማውን ለማሳካት ሲል
በሀገሪቱ ባሉ ተቋማት በሙሉ ቁልፍ ቁልፍ ቦታዎችን በህወሐት ካድሬዎች
እንዲያዙ ያደርጋል፡፡ በብዙ ተቋማት ደግሞ ቁልፍ ቁልፍ ቦታዎችን ብቻ ሳይሆን ከላይ
እስከታች ያለውን ቦታ በእነዚህ የአንድ ብሔር ድርጅት ካድሬዎች
ተይዞ ይገኛል፡፡ የፌዴራል ተቋም ሆኖ ሳለ የሚመስለው ግን የአንድ
ክልል ተቋም ነው፡፡ ከእነዚህ ተቋማት ውስጥ በፌዴራል ማረሚያ ቤት ሥር
ያሉት የቃሊቲ፣ ቂሊንጦ፣ ዝዋይ፣ ሸዋ ሮቢትና የድሬደዋ እስር ቤቶች
ይገኙበታል፡፡ በእነዚህ እስር ቤቶች የሚፈፀመው ዘረኝነት ተመሳሳይነት
ቢኖረውም በቃሊቲና ቂሊንጦ እስር ቤቶች የሚፈፀመው ግን እጅግ የከፋ
ነው፡፡ በሌሎች ያለውን ለጊዜው እንተወውና ለዛሬ በቂሊንጦ እየተፈፀመ ያለውን ላውጋችሁ፡፡

 በቂሊንጦ ከባድ ጥበቃ ማ/ቤት የመምሪያ ኃላፊዎች፣ የክፍል ኃላፊዎች፣ የሦስቱም ዞኖች
ኃላፊዎች ሙሉ በሙሉ የህወሐት ካድሬዎች ሲሆኑ ጥበቃዎች፣ ቤተሰብ አገናኞችና ሌሎችም የሥራ ቦታዎች
ከሞላ ጎደል በእነርሱ የተያዙ ናቸው፡፡ ይህ የቂሊንጦ እስር ቤት በ3 ዞኖች የተከፈለ ነው፡፡
በእነዚህ ዞኖች እየተፈፀመ ያለው የዘረኝነት ተግባር ተመሳሳይ ቢሆንምበዞን ሁለት እየተፈፀመ ያለው ግን
ከሁሉ የከፋ ነው፡፡
በዚህ ዞን ከ15 ዓመት እስከ ሞት ድረስ ያሉ ፍርደኞች የሚታሰሩበትቦታ ነው፡፡
በዚህ ዞን ብዙ የፖለቲካ እስረኞች ይገኛሉ፡፡ በግንቦት 7፣ በኦነግ፣
በኦብነግ፣ በአርበኞችና በሌሎች የተከሰሱ እስረኞች ይገኙበታል፡ ፡ ከእነዚህ የፖለቲካ እስረኞች ጋር
ሰላምታ የተለዋወጠ፣ያወራ፣አብሮ የሄደና ማንኛውንም ማህበራዊ
ግንኙነት የፈጠረ እስረኛ ቢሮ እየተጠራ ዛቻ ፣ማስፈራራትና ድብደባ
ይፈፀምበታል፡፡ በተለይ በግንቦት 7 እና በኦነግ ከተከሰሱ እስረኞች
ጋር የሚቀራረቡ የአማራና የኦሮሞ ተወላጆች ቁም ስቃያቸውን ነው
የሚያዩት፡፡ በዞኑ ብዛት ያላቸው ወሬ አቀባዮች ወይም በእስር ቤት ቋንቋ
አስጠጪዎች ያሉበት ቦታ ነው፡፡
እነዚህ ደግሞ የእነርሱ ብሄር አባላት ናቸው፡፡ እነዚህ ከሌላው በተለየ መልኩ
የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞችን እንዲያገኙ ይደረጋል፡፡
ክበቡን፣ህብረት ሱቁን እንዲይዙ ይደረጋል፡፡ በእስር ቤቱ ያልተፈቀዱ
ነገሮች (ሲጋራ፣ ጫት፣ አደንዛዥ ዕፅ ወዘተ...) እንዲያስገቡና እንዲሸጡ
ይመቻችላቸዋል፡፡ የሚያገኙትንም ጥቅም ከኃላፊዎች ጋር ይጋራሉ፡፡
በነፃነት የፈለጉበት ቦታ ሄደው የመምጣት፣ ከተማ ሄደው የመዋልና
ጉዳያቸውን የማስፈፀምና የተለያዩ መብቶች ተሰጧቸዋል፡፡ እነዚህ
አስጠጪዎች የፖለቲካ እስረኞችን በመከታተል ከእነርሱ ጋር የተገናኘን
ማንኛውም እስረኛ እየመዘገቡ ወደ ቢሮ
ያስተላልፋሉ፡፡ባስተላለፉትም መሠረት እየተጠሩ ዘግናኝ ማስፈራሪያና ድብደባ
ይፈፀምባቸዋል፤ በካቴና እጃቸውና እግራቸው እየታሰሩ ለሳምንታትና
ለወራት እንዲቆዩ ይደረጋል፡፡ በየሳምንቱ በሚደረግ የቤት ውስጥ
ግምገማ ወይም የዞኑ አጠቃላይ ስብሰባ ላይ አሰራራቸውን የሚነቅፍ አስተያየት
የሰጠ እስረኛ “አንተ የግንቦት 7 ወይም ኦነግ ነህ” በማለት የሚያሰቃዩት እስረኛ
ብዙ ነው፡፡ በቅርቡ ያሬድ ሺፈራው የተባለውን እስረኛ ከግንቦት 7 ሰዎች
ጋር ቅርርብ አለህ በማለት በተደጋጋሚ እየጠሩ ሲዝቱበትና ሲያጨናንቁት ከቆዩ
በኋላ አንድ ቀን ጠርተው ነገ በሚኖረው ስብሰባ ላይ “የግንቦት 7 አባል ነኝ፡፡
ይህንን ያንን አድርግ ብለውኝ ነበር” ብለህ ተናገርና እንተውሃለን ሲሉት እሺ
ብሏቸው ወጣ፡፡ በኋላም በስብሰባው ላይ እንዲነሳና እንዲናገር ሲያደርጉት “እኔ
እናቴ ያሬድ ብላ ነው ስም ያወጣችልኝ አሁን ግን እናንተ ግንቦት 7 ብላችሁ
ስም አወጣችሁልኝ” ብሎ ሊቀጥል ሲል አስቆሙት፡፡ በኋላም ከዚያ ዞን
አንስተው እስካሁን የት እንዳደረሱት አይታወቅም፡፡ እንዲሁም አሸናፊ
የተባለ እስረኛ በማንነቱ ብቻ ከቆጠራ በኋላ አስወጥተው ከባድ ድብደባ
ፈጽመውበታል፡፡
በተመሳሳይም ዮናስ አስፋው በተባለው እስረኛ ላይም ከባድ ድብደባ ተፈጽሞበታል፡፡
 እንዲሁምብዛት ያላቸው የአማራና የኦሮሞ ተወላጆች ላይ ወከባ፣ ዛቻና ማስፈራሪያ
ከፈጸሙ በኋላ 13ቱን የካቲት 22 ቀን 2005 ዓ.ም ወደ ዝዋይ በመጫን እዚያ
በሚገኘው የጨለማ ቤት እያሰቃዩአቸው ይገኛል፡፡
እነዚህም፡-
1.ስሜነህ ምትኩ
2.አምባቸው ዘሪሁን
3.አንተነህ አምፖሎ
4.ሰይድ ሁሴን
5.ናደው ፍርዴ
6.ካሳሁን አብደላ
7.ዮርዳኖስ ግርማ
8.ደ/አዝማች በየነ
9.አለነ ብላታ
10.ገብሬ ሲሳይ
11.ዮናስ አስፋው ይገኙበታል፡፡
በህገ መንግሠቱ ላይ “ማንኛውም እስረኛ ለቤተሰቡ ቅርብ በሆነ እስር
ቤት እንዲታሰር ይደረጋል“ ተብሎ የተቀመጠ ሲሆን እነዚህንና ሌሎች
ብዛት ያላቸውን እስረኞች ወደ ዝዋይ የሚጫኑበት ምክንያት ከዘረኝነት
የመነጨ ጥላቻቸው መገለጫ ነው፡፡ እነዚህን እስረኞች ከቤተሰቦቻቸው
በማራቅ ለማጨናነቅና የሚደርሱባቸውን ተፅዕኖዎች እንዳይታወቁ
(ወደ ሕዝቡ እንዳይደርሱ) ከአዲስ አበባ ማራቁ እንደ መፍትሄ ስለሚወሰድ ነው፡፡
ከግንቦት 7 ጋር በተያያዘ ተከሰው በእስር ቤት ከሚማቅቁት ውስጥ፡
1.ብ/ጄኔራል ተፈራ ማሞ
2. አሳምነው ፅጌ
ቃሊቲ በሚገኘው የብቻ ማሰሪያ ክፍል ውስጥ 3 ዓመት ከ8 ወራት
ሲሰቃዩ ከቆዩ በኋላ ለብዙ ቀናት እጅና እግራቸውን በካቴና አስረውና የቤተሰብ
ግንኙነት ከልክለው ወደ ዝዋይ እስር ቤት ጭነዋቸዋል፡፡
በተጨማሪም በተመሳሳይ ክስ ከተከሰሱት ውስጥ፡-
1.ሌ/ኮ ደምሰው አንተነህ
2. ሌ/ኮ ዓለሙ ጌትነት
3. ሌ/ኮ ሰለሞን አሻግሬ
4. ሻለቃ መኮንን ወርቁ
የተባሉትን የካቲት 22 ቀን 2005 ዓ.ም ወደ ዝዋይ ጭነዋቸዋል፡፡
እዚህ አ/አ በሚገኘው ቃሊቲና ቂሊንጦ እስር ቤት ከአንድ ዞን ወደ
ሌላ ዞን እንዲሁም ወደ ጨለማ ቤት እያዘዋወሩ ሲያሰቃዩአቸው የነበረ
ሲሆን በተደጋጋሚ በተለያየ ጊዜ እየጠሩ “በጥይት እንደበድባችኋለን“፣
“የመጀመሪያው ጥይት እናንተ ላይ ነው የምናሳርፈው“ ወ.ዘ.ተ እያሉ
ይዝቱባቸው ነበር፡፡ ይህ ሳያንስ ከሚስቶቻቸውና ከልጆቻቸው በማራቅ
ዝዋይ በሚገኘው ልዩ ቤት አጉረው እያሰቃዩአቸው ይገኛሉ፡፡
በተመሳሳይም
1.አቶ በቀለ ገርባ
2.አቶ ኦልባና ሌሊሳ
የተባሉ የኦፌኮ/መድረክ አመራሮችን ቃሊቲ በሚገኘው የጨለማና ልዩ እስር
ቤት ውስጥ ካሰቃዩ በኋላ ወደ ዝዋይ ጭነው እዚያ ባለው ልዩ እስር ቤት
ውስጥ ይገኛሉ፡፡ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የፖለቲካ እስረኞችንና በበማንነታቸው ብቻ
የአማራና የኦሮሞ ብሄር ተወላጆችን  ወደ ዝዋይ በመጫን ከቤተሰቦቻቸው
በማራቅና በዝዋይም የተለያዩ ጫናዎችን በመፈፀም ላይ ይገኛሉ፡፡ ከጊዜ ወደ
ጊዜም ይህን ድርጊታቸውን አጠናክረው እየቀጠሉበት ይገኛሉ፡፡ ምንም እንኳን
ለነዚህ ተቋማት ማረሚያ ቤት የሚል ስም የሰጧቸው ቢሆንም እውነታው
ግን ከዚህ በፍፁም የተለየ ነው፡፡ አንዳችም የማረምና የማነፅ ተግባር
የሚካሄዱባቸው ተቋማት አይደሉም፡፡ ይልቁንም ከተቆራኛቸው የዘረኝነት አባዜ
በመነጨ እስረኞችን በማንነታቸውና በፖለቲካ አቋማቸው በእስር ቆይታቸው
ማጨናነቅ፣ ማዋከብ፣ አየጠሩ ማስፈራራት፣ ቤተሰቦቻቸው ላይ ጫና
መፍጠር፣ ከቤተሰቦቻቸው በማራቅ ግንኙነታቸውን ማዳከምና ከተቻለም
ማቆራረጥ እንደ ፖሊሲ ይዘው እየተገበሩት ይገኛል፡፡
ከግንቦት 7 ጋር በተያያዘ የታሰሩት እስረኞች ከቤተሰብ ጋር በሚገናኙበት
ወቅት የህወሓት አባላት የሆኑ ፖሊሶች ብቻ ተመርጠው ከጎናቸው ስለሚቆሙና
ለደቂቃም ያህል ስለማይለዩ ቤተሰባዊ ሚስጥሮችን(ጉዳዮችን) እንኳን
ለማውራት አስቸጋሪ ነው፡፡
በጭውውት ውስጥ መንግስትን ይነካል የሚሉት አረፍተ ነገር ከሰሙ
ዛቻውና ማስፈራሪያው ይህ ነው የሚባል አይደለም፡፡ በእስር ቤቱ
የሚሰጡ ማንኛውንም አገልግሎቶች (ዝውውር፣አመክሮ፣ይቅርታ፣የፍ/ቤት
ጉዳዮች፣ልዩ ልዩ ወ.ዘ.ተ) ለማግኘት ማንነትህ ወሳኝ ነው፡፡ ወይ የነሱ ሰው
መሆን አለብህ ካልሆነ ደግሞ ገንዘብ በደንብ ሊኖርህ ይገባል፡፡
በአጠቃላይ በዚህ እስር ቤት ውስጥ ዘግናኝ የሆነ የሰብዓዊ ጥሰት ያለበት፣
በማንነቱ ብቻ እስረኛው ቁም ሥቃዩን የሚያይበት ቦታ ነው፡፡ ሰውን ማሰር ብቻ
ሳይሆን አሥረውም ካላሰቃዩ ካላንገላቱ እርካታ የማይሰማቸው ዘረኞች የበዙበት
እስር ቤት ነው፡፡ ዓላማቸው ከእነርሱ ውጭ ያሉ ሕዝቦችን በእስር በማሰቃየት ቢቻል
መግደል ካልሆነም በቁሙ መግደል ነው፡፡ የሚገርመው ደግሞ የሚቆጣጠራቸው
አካል ያለመኖሩ ነው፡፡ ለስሙ ከፌ/ ማ/ቤ ኮሚሽን እና መንግስታዊ
ያልሆኑ ድርጅቶች ነን ባዮች ነገር ግን ከራሱ ከመንግስት በላይ ለመንግስት
የሚቆረቆሩ ካድሬዎች የሆኑ የእነ ፓስተር ዳንኤል ገብረ ሥላሴ አይነት
ድርጅቶች ለተለያየ ጊዜ እስር ቤቱን ቢጎበኙም ከተቆርቋሪነታቸው የተነሳ
እስር ቤቱን አድንቀውና አወድሰው ከመሄድ ባለፈ እውነታውን ማወቅም
ሆነ ማሳወቅ አይፈልጉም፡፡
ችግራችንን የሚያይልንና መፍትሄ የሚሰጠን አካል ባለማግኘታችን ይኸው
ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ስቃያችንን እንዲያውቅልን ስንል እውታውን
በጥቂቱም ቢሆን ልናሳውቅ ተገደናል፡፡
ፍኖተ ነጻነት