Mar 20, 2013

አራት አንጋፋ የህወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት በክብር ተሰናበቱ


ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አ.ማ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 11 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) ለቀናት ጉባኤውን ሲያካሂድ የሰነበተው የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ህወሃት በማጠናቀቂያው የፓርቲውን 45 የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ምርጫ እያካሄደ ይገኛል ።
ለዓመታት ፓርቲውን በማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ያገለገሉት አምባሳደር ስዩም መስፍን ፣ አምባሳደር ብርሃነ ገብረክርስቶስ ፣ አቶ አርከበ ዕቁባይና አቶ ዘርዓይ አስገዶም ባቀረቡት ጥያቄና ፓርቲው እየተገበረ ባለው የመተካካት ሂደት መሰረት በአዲስ አባላት እንዲተኩ የወሰነ ሲሆን አንጋፋ አባላቱ በክብር ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ተሰናብተዋል።
ላመንበት ዓላማ በመታገላችንና በመስራታችን አሁን ደግሞ በክብር በመሰናበታበታችን ክብር ይሰማናል ብለዋል አንጋፋ አባላቱ ።
የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ምርጫው ተካሂዶ የድምፅ ቆጠራ እየተከናወነ ይገኛል ።


No comments:

Post a Comment