Jan 30, 2013

አቶ አሊ አብዶ ስዊዲን ደርሰዋል/ኢሳያስን ከድተዋል

የኤርትራውየማስታወቂያ ሚኒስትር የነበሩት አይቶ አሊ አብዶ አህመድ ሃገሪቱን ለቀው ወጥተዋል የሚኖሩትን በስዊዲን በምስጢራዊ ቦታ ነው ሲል  Expressen የተባለ የስዊዲን ጋዜጣ ዘገበ::ለጛዜጣው ሪፖርተር ቃሲም ሃማዴ ጋር ቃለምልልስ አድርገዋል::

አቶ አብዱ እንዳሉት በኤርትራ እስር ቤት የሚገኘውን ዳዊት ኢሳቅ ምን አይነት ሁኔታ ላይ እንዳለ የስዊዲን መንግስት አለመጠየቁ እንደገረማቸው አስታውቀው ለቤተሰቡ ግን ምኒም ተስፋ ለመስጠት አልደፍርም ብለዋል::በህይወት መኖሩን እየተጠራጠሩ::
የ47 አመቱ አሊ አብዱ በኖቮምበር ወደ ጀርመን ለስራ ጉድይ ከሄዱ በሁዋላ አልታዩም ነበር...እኚህ የኢሳያስ ለረዥም አመታት የቅርብ ሰው የሆኑት ሲለሳቸው ሚኒም ነገር አልተሰማም ነበር...ለጋዜጠኞችም ለመናገር አልደፈሩም ነበር...ቢሆንም አሜሪካን አገር ከሚኖሩት በወንድማቸው በአይቶ ሳላህ የሱፍ አማካኝነት ለስዊዲን ጋዜጣ ቃለምልልስ ሰተዋል::
ማንኛውን ሰው ካለፍርድ ቤት ትዕዛዝ እና ካለ ማስረጃ በስልክ በሚሰጥ ትዕዛዝ ነው የሚያዘው ያሉት ሚኒስትሩ ከምዕራባውያን የደህንነት ሰዎች የሚመጣውን ጥያቄ በመፍራት የሚደረግ ሲሆን....ዳዊት ይሳቅን ጨምሮ ሌሎች የፖለቲካ እና የህሊና እስረኞች የት እንዳሉ ማንም አያውቅም ብለዋል::ለመጠየቅም የሚደፍር የለም ሲሉ አክለውበታል::በሃገሪቱ የጉረላ/ደፈጣ አይነት የፖለቲካ ባህል ያለ ሲሆን ማንኛውም ትዕዛዝ ሲመጣ ለምን ሳትል መፈጸም አለብህ ሲሉ ተናግረዋል::
በፖለቲካ እስረኞች ላይ ምን እንደተፈፀመ እንደማያውቁ እና ይህንን የሚያውቀው ፕረሲዳንት ኢሳያስ እና የደህንነት መዋቅሩ ብቻ ነው ብለዋል::የፖሊስ አዛዦች እንኳን ይህን አያውቁም::
አገሪቱን ለቀው ከወጡ ከኖቨምበር ጀምሮ አባታቸውን ጨምሮ ወንድማቸው እና የ15 አመት ሴት ልጃቸው በደህንነት ሃይሎች ተይዘው የት እንዳሉ አይታወቅም::

በአሜሪካ የሚኖሩት ወንድማቸው ሳላህ የኑስ ወንድሜ ለመጪው የኤርታር ትውልድ ያለውን መጨነቅ እና ፍራቻ ስሜቱን ረብሾታል ብለዋል::


ENGLISH TRANSLATION 

No comments:

Post a Comment