Feb 1, 2013

በዱባይ የሚኖሩ 5 ነጋዴዎች ለአዳነ ግርማ መኪና አበረከቱለት


ኢሳት ዜና:-በዱባይ የሚኖሩ አምስት ኢትዮጵያውያን ነጋዴዎች  የ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን  ኮከብ ተጫዋች ለሆነው አዳነ ግርማ  ቶዮታ ኮሮላ መኪና  ገዝተው ሰጡት።
ኢትዮጵያውያኑ ነጋዴዎች  ለ አዳነ ግርማ የመኪና ስጦታ ያበረከቱለት  ከሰላሳ አንድ አመት  በሁዋላ ኢትዮጵያ ለኣፍሪካ ዋንጫ አልፋ  ባደረገችው ውድድር ጎል ከማስቆጠሩና ኮከብ ተጨዋችነቱን በማስመስከሩ ነው።
ለአዳነ ግርማ የመኪና ስጦታ ያበረከቱለት ፦አቶ ጌታቸው ሙሶኮሬ ፥ አቶ ይልማ ተፈራ፥ ወ/ሮ ቀለም ተክሉ፥ አቶ መሃመድ የሱፍ እና ወ/ሮ ህሊና ነጋሽ የተባሉ ነጋዴዎች ናቸው።
ከዛምቢያ ጋር በተደረገው ጨዋታ ኮከብ ሆኖ የታየውና ቡድኑን አቻ ያደረገችውን ጎል ያስቆጠረው አዳነ፤ኢትዮጵያ ሁለተኛ ጫዋታዋን ከቡርኪናፋሶ ጋር ስታደርግ ዘጠነኛው ደቂቃ ላይ ተጎድቶ መውጣቱ፤ በቡድኑ አጨዋወት ላይ ክፍተት  ከመፍጠሩም በላይ በተጫዎቹም ዘንድ አለመረጋጋትን አስከትሎ እንደነበር ይታወሳል።

No comments:

Post a Comment