Feb 19, 2013

ይች ሀገር የት ናት!!!!!

ውሸት ተደማጭነት ካገኘ 21 ዓመታት አስቆጥሮ ሕዝብን ያሰለቸ ከመሆኑ ባሻገር ወያነን እርቃኑን እንዳወጣ ገና አልተረዱም ምክንያቱም ውሸታቸው የተራመደውን ያህል እንድተበላ ጎማ መላላጡንና አሻራም እንድሌለው አይናቸውን ጭምር ደፍኖት አይምሮአቸውን አሻግቶት ሕሊናቢስነታቸውና ሰውነታቸውን እንደዘነጉ መንገዱም መጨረሻቸው ለመሆኑ ከእለታዊ ምግባራቸው እያስመሰከሩ ነው፡
ነገርግን አንድ የሚያሳስብና የሚያስጨንቅ ራሴንና ሌላውንም ወገኔ ምን እያሰብ መሆኑን ለመረዳት እያቃተኝ ነው ኢትዮጵያውያን የሙስሊም እምነት ተከታይ ወንድሞቻችን፡ የመብት ጥያቄ የእምነት ጥያቄ የኛም ክርስቲያኖች ጥያቄ በመሆኑ የትግሉ አጋሮች በመሆን በውህደት የኛንም ታሪካዊና ጥንታዊ ኦርቶዶክስን የማዳን ኃላፊነት አለብን ታድያ ምን ለመጠበቅ ነው በፍራቻና በጥርጣሬ ከዳር በመቆም የወያነን የማስፈራርያ ውሸት በመመራት የተነሱበትን ድምፃችን ይሰማ ጥያቄ የታሰሩት መፍትሄ አፈላላጊ ሽማግሌዎች በሕብረት በመቆም ይህ ጥያቄ መልስ እንዲያገን ለማድረግ ሌሎቹንም ጥያቄዎች እንዲመለሱልን የፍርሃት ብልኮአችንን አውልቀን እንደወንድሞቻችን በትባትና በቆራጥነት ወያነን ይበቃል በማለት መነሳት ይኖርብናል፡ ላለፉው አንድ ዓመት በመታሰር በሞሞት በመሰደድ የጠፋው ሁሉ የእስልምናን እምነት ብቻ ያዘለ ሳይሆን መብታችን እምነታችን ይጠበቅ በመሆኑ የሁላችን አድርገን መነሳት ተገቢ ነው፡
ጎርፉ ተሯሯጠ ጊዘውነው መሰለኝ
ሕዝቡ ነቃ ድምጹን አሰማ መገዛት መረረኝ
ጥላቻ ብቀላ በጥቂት ሆዳሞች
አብቃለት ውሸት የበረከት ድርሶች
የጎሳ ባንዲራ የጽንፈኞች መዝሙር
ብቀላ አድርባይ የነበረው አጥር
ፈረሰ በሕዝቦች ሰላምን በሚጥር
ተጋለጠ ሴራ ግድያ መፈክር
ከላይ ከእርካኑ የዘቀጠ በውሸት
አሸባሪ ሆኖ በራሱላይ ሁከት
ልማት በሌለበት በዘራፊዎች ሰአት
ከሸፈ በንቃት የወያኔ ምታት
አስርበው ጨቁነው ለመግዛት
ሕዝብን በማጋጨት ፈረዳአቅቸው ውድቀት
ሕጋቸው አይጸና ተለዋጭ በለት
ሹመኛው አድርባይ የሌለው ብቃት
ውሸት ውሸት ከመሆን ያለማለፉ እየታየ በመሆኑ፤ሊያደርጉ የማችሉትን በጥቂት ከማን እንደተወለዱና እናት ይሁን አባት የማያውቁ ወንድምና እህት ፍቅር ምነን እንደሆነ የማይገባቸው ለፍጥረት ዴንታ የሌላቸው ጥቂት የወያኔ የአጋዚ አንጋቾች በጭካኔ ያለርህራሄ የሚያደርጉት ተግባር ሳንብረከረክ በትባት እጅ ለእጅ ተያይዘን እናምክናቸው ጣልያን የተሸነፈው በመሳራ እጦት ሳይሆን በቆራጥነት ሃገራዊ ራኢ የሌለው በመሆኑ እኛ ግን አጋዚን የምንዋጋው በሀገር ፍቅርና በሃይማኖት ጽናት በመቆም ስለሆነ የድሉ ባለቤቶች ነን።
ድል ለመላው የመብት ተከራካሪዎች ለ እውነትና ለሃገር ለወግን የቆሙ በሙሉ
ውድቀት ለሆድ አደሮችና ከፋፋዮች
ኢትዮጵያ በነጻነቷ ለዘላለም ትኑር

No comments:

Post a Comment