Feb 19, 2013

በእነ አቶ በረከት/በኢህአዴግ ያኮረፉ ባለሥልጣናት ወደ ጎራው መቀላቀላቸውን ቀጥለዋል


junedinsado(ከተበዳይ ኮሚኒኬተሮች የተጻፈ ዜና) በኢህአዴግ ከአሸባሪዎች ጎራ ሊቀላቀል ሴራ እየተሸረበላቸው ያለውና በዚህም በእጅጉ ያኮረፉት የቀድሞው የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር
 ሚኒስትር አቶ ጁነዲን ሳዶ የተበዳይ ኮሙኒኬተሮችንና ያኮረፉ ባለሥልጣናትን ጎራ ለመቀላቀል ያቀረቡት ጥያቄ በጥምረቱ ጥምር ኮሚቴ ውድቅ ተደረገ፡፡ ባለፈው ሳምንት የተበዳይ ኮሚዩኬተሮችና ያኮረፉ ባለስልታናት ጥምረት ኮሚቴ ለአቶ ጁነዲን ምስጢራዊ ሰነዶችንና ዶክመንቶችን እንዲሁም የሚያውቁትን የኢህአዴግ ምስጢር ሁሉ በምስልም ሆነ በድምጽ እነዲሰጧቸው ጥያቄ አቅርቦላቸው ነበር፡፡ አቶ ጁነዲንም በምስጢር በተወካዮቻቸው በኩል የተበዳይ ኮሙዩኬተሮችንና ያኮረፉ ባለስልታናትን ጎራ መቀላቀል ትግሉንም መምራት እንደሚፈልጉ፣ ስለጠየቁት ምስጢራዊ መረጃም ያላቸውንና የሚያውቁትን በሙሉ እንደሚሰጧቸው አረጋግጠዋል፡፡
አቶ ጁነዲን እንዳሉትም በተለይ በአሁኑ ሰዓት ኢህአዴግ ሊያስራቸው እየተንቀሳቀሰ በመሆኑ ወህኒ ከመውረዳቸው በፊት በእጃቸው ያለውንና የሚያውቁትን ምስጢራዊ መረጃ ሁሉ ለተበዳይ ኮሚኒኬተሮችና ላኮረፉ ባለስልጣናት ጥምረት በአስቸኳይ አሳልፈው መስጠት እንደሚፈልጉ ገልጸውላቸዋል፡፡ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥም መረጃውን ሊያስረክቡአቸው እንደሚችሉም ቃል ገብተዋል፡፡ ወደ ተበዳይ ኮሚኒኬተሮች ጎራ ተቀላቀሉም አልተቀላቀሉም መረጃውን ለማስረከብ ጊዜ መውሰድ እንደማይፈልጉም ተናግረዋል፡፡ (በነገራችን ላይ በኢህአዴግ ያኮረፉ ባለስልጣናት በአግር ውስጥም በውጭም የሚገኙ ሲሆን አብዛኞቹም ኢህአዴግነት የተሰናበቱ ናቸው፡፡ ከዛው ሆነው ከውስጥ የሚታገሉም አሉ፡፡)
ሆኖም ግን የተበዳይ ኮሚዩኬተሮችና ያኮረፉ ባለስልታናት ጥምረት ኮሚቴ የአቶ ጁነዲንን የመቀላቀል ጥያቄ አልተቀበለውም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የአቶ ጁነዲን ጉዳይ ከአሸባሪነት ጋር ስለሚያያዝና ይሄኛው ትግል ግን ዛሬ ለጥንቃቄ ሲባል ምስጢራዊ ቢሆንም ነገ በሰላማዊ መንገድ በአገር ውስጥ መታገል  የሚፈልግ ከመሆኑ ጋር የተያያዘ ነው ተብሏል፡፡ እናም የአቶ ጁነዲንን ወደ ጎራው የልቀላቀል ጥያቄ ለጊዜው አንቀበልም በለዋል፡፡ ይህ  የተበዳይ ኮሚዩኬተሮችና ያኮረፉ ባለስልታናት ጥምረት  በቂና አስተማማኝ መረጃ ካገኘ በሁዋላ በተለያዩ መንገዶች ለህዝቡ በስሙ በተዘጋጀ ዌብሳይትና በሌሎች የሚዲያ ዘዴዎች በመጠቀም የሚያሰራጭ ይሆናል፡፡
ይህ በእነዲህ እያለ አቶ ጁነዲን ሳዶ በሰሞኑ የአርሂቡ መጽሔት ላይ በተነበበው መሰረት በተለይ የሚታሰሩ ከሆነ ምስጢር እንደሚያወጡ ኢህአዴግን አስጠንቅቀዋል፡፡ እንደ አርሂቡ መጽሄት ዘገባ ከሆነ አቶ ጁነዲን ማነኛውንም መንግስታዊ/ኢህአዴግአዊ  ምስጢር ለማውጣት ማንንም እንደማይፈሩ ገልጸዋል፡፡ በተለይም እርሳቸውን ለማሰር የሚደረገው እንቅስቃሴ ካለልቆመና በሰላም ለመኖር የማይችሉ ከሆነ ምስጢር ለመማውጣት ወደሁዋላ እንደማይሉ ነው የተነናገሩት፡፡ አለኝ የሚሉትን ምስጢራዊ መረጃም ለየተበዳይ ኮሚዩኬተሮችና ያኮረፉ ባለስልታናት ጥምረት ኮሚቴ አሳልፈው እንደሰጡ የሚያሳይ ዘገባ ነው አርሂቡ ያስነበበን፡፡
በሌላም መልኩ ባለፈው ቅዳሜ ለንባብ የበቃችው ቆንጆ መጽሔት አቶ ሬድዋንና አቶ በረከት ለኢህአዴግ የማታለልና የማስመሰል ጉዞ እንደማሳያ በሚል ርእስ ባስነበበችው መሰረት አቶ በረከት ኮሙኒኬተሮቻቸውን በከፍተኛ የደሞዝ ልዩነትና በልዩ ልዩ ጥቅማጥቅሞች ከፋፍለው እንደሚያስተዳድሩና በዚህም በየፌደራል መስሪያ ቤቱ የሚገኙ ኮሙኒኬተች የተለዬ ቡድን መስርተው እይተንቀሳቀሱ እንደሆነ፣ የተለያዩ ምስጢራዊ መረጃዎችንም ሊለቁ በዝግጅት ላይ እንደሆኑ የሚያሳይ ዘገባ ተዘግቧል፡፡ አቶ በረከትም ከመንግስት የተሰጣቸውን የምንግስት ኮሚኒኬተሮችን የማሰልጠንና የማብቃት ሚና እየተወጡ እንዳልሆነና ምንግስትንም/ኢህአዴግንም እያታለሉ እንደሆነ ተገልጾአል፡፡
አቶ በረከት ለኮሙዩኒኬተሮቻቸው የሚያሳዩት ንቀትና የማታለል መንገድ አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡ በዝምታቸው ቀጥለዋል፡፡ የተለመደው ሥልጠናው ነገ፣ በሚቀጥለው ሳምንት፣ ወዘተ ይሰጣል የሚለው የእነ አቶ በረከትማስመሰያና ማባበያቸውም ቀጥሎአል፡፡ የተበዳይ ኮሙዩኒኬተሮች ዝም ማለት ግን የእነ አቶ በረከትንና የድርጅታቸውን ገመና የበለጠ ለመሰብሰብና መረጃን በበቂ ሁኔታ ለማጠናከር እነደሆነ ከኮሚቴው ውስጥ ያሉ ሰዎች ገልጸውልናል፡፡ እንዲያውም የእነ አቶ በረከት ንቀትና ማስመሰል እንዲሁም እንደህጻን መደለል እጅግ እንዳበሳጫቸውና ለበለጠ ክፋት እንዳነሳሳቸው አስረድተዋል፡፡ ጉዳዩንም በበሳል አመራር ለመምራት እየሰሩ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ምንም ድምጽ ሳያሰሙና ሳያስነቁ ባልታሰበና ባልተጠበቀ መልኩ አደጋ ለመጣል ነው እንቅስቃሴአቸው፡፡ ምንም አያመጡም በማለት በንቀት ለሚመለከቷቸው አቶ በረከትም ምንም አለማምጣታችንን እናሳያለን ብለዋል፡፡ ውስጣቸውም ለከፍተኛ በቀል እንደተነሳሳና ከምንም በላይ አቶ በረከትና ጽ/ቤታቸው ላሳዩአቸው ንቀትና ማታለል መበሳጨታቸውን ገልጸው በምሬት ነግረውናል አስተባባሪዎቹ፡፡
ሁሉም ተበዳይ ኮሙኒኬተር ብቻ ሳይሆን በኢህአዴግ የመከፋፈልና የአድሎ አመራር የተማረረ ዜጋ ጎራቸውን እንዲቀላቀል አሳስበዋል፡፡ የባለስልጣናትና ከፍተኛ አመራሮች ቁጥርም እየቸመረ መሆኑንና የአመራር ቦታውንም እያጠናከሩ መሆኑን ገልጸውልናል፡፡ በተለይ ኮሙኒኬተሮች ለዚህ ትግል እንዲታጠቁ፣ መረቡንም እስከ ወረዳ ድረስ እንዲዘረጉ አሳስበዋል፡፡ ወደ ጎራው ለመቀላቀልም ከፈለጉ አስተባባሪዎች አድራሻቸውን በሚስጢር እያሳውቁ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ለማነኛውም ለሚያደርጉት ትግል ፈንድ እያገኙና የበጀት ችግርም እንደማይገጥማቸው ገልጸዋል፡፡ እናም አሁን የእነ አቶ በረከትን ሥልጠናም ሆነ ጥቅማጥቅም እንደማይጠብቁና በራሳቸው መንገድ ግን የእነርሱን ብቻ ሳይሆን የአገሪቱን ምስኪን ዜጎች መብት ለማስጠበቅ እንደሚታገሉ ገልጸዋል፡፡ ቀጣይ እርምጃቸው መቼና ምን እንደሚሆን ግን ከመግለጽ ተቆጥበዋል፡፡ ይህም ሚስጢር ነው ብለዋል፡፡
የእኛንም አስተያየት እንጨምር፡፡ ይህ የኮሙኒኬተሮች ጉዳይ እነ አቶ በረከትን ብቻ የሚመለከት አይመስለንም፡፡ ኢህአዴግም ቆም ብሎ ቢያስብበት መልካም ነው፡፡ ሠራተኛን መናቅና መከፋፈል ሁሌ መጨረሻው ያው መከፋፈልና ጥፋት ነው፡፡ መከፋፈሉ የሚጎዳው እነ አቶ በረከትን ሳይሆን አገርን ሊሆነ እንዳይችል መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ መረጃዎችም የብሄርና የሃይማኖት ግጭት የሚያስከትሉ እንዳይሆኑ መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ የኢህአዴግ አመራርም ለምን ዝም እንደሚል ግልጽ አይደለም፡፡ ይህ ተራ ነገር ነው ብሎ ብቻ መቀመጥ ሳይሆን ሠራተኛን በአግባቡ መያዝ ሳይሻል አይቀርም፡፡ ለማነኛውም መረጃው የገር ጥፋት የማያስከትላና ኢህአዴግን ብቻ የሚጎዳ ቢሆን መልካም ነው፡፡ አቶ በረከትን ለመበቀል ሲባል አገር እንዳይበትን ጥንቃቄ……..

No comments:

Post a Comment